በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የሚገኙ የሰንበት ትምህርት ቤቶች የማጠቃለያ ፈተና  ተሰጠ

በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሥር በሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በሀገረ ስብከቱ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት አስተባባሪነት አዲሱን ሥርዓተ ትምህርት ተግባራዊ ባደረጉ ሰ/ት/ቤቶች ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የቆየው ማጠቃለያ ፈተና በዛሬው ዕለት በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።

በሀገረ ስብከት ደረጃ 2014 ዓ.ም የአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ማጠቃለያ በደመቀ ሁኔታ በደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት ጊዜያዊ የመሰብሰቢያ አዳራሽ መሰጠቱንም ነው የተገለጸው።

በፈተና ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ንቡረ ዕድ ቆሞስ አባ መዘምር አሰግደው ፣የሀገረ ስብከቱ ሰንበት ት/ቤት ማደራጃ ክፍል ሓላፊ መጋቤ ሃይማኖት ቀሲስ አብርሃም ሙሉጌታ እንዲሁም የሀገረ ስብከቱ ትምህርት ክፍል ሓላፊ ሊቀ አዕላፍ ቀሲስ ዮርዳኖስ አቢ በተገኙበት በተሳካ ሁኔታ መካሄዱን ከሀገረ ስብከቱ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ይፋዊ ፌስቡክ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።