እንደሚታረዱ በጎች ሆንን!

እንደሚታረዱ በጎች ሆንን!

እንደሚታረዱ በጎች ሆንን!

እንደሚታረዱ በጎች ሆንን!

ኢትዮጵያ አገራችን ለረጅም ዘመናት በአኩሪ ባህልና እሴት አሸብርቃ ከእኛ ደረሰች ናት። ለዚህ መልካም እሴት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሚና ጉልህ ነው። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን ወርቅ ላበደረ ጠጠር እንዲሉ ቤተ ክርስቲያን የጥቃት ዒላማ ሆና ብዙ ቀስቶች ሲወረወሩባት ታያል። መንግሥትም አጥፊዎች ላይ ርምጃ ከመውሰድ ይልቅ የጥፋቱ አካልና ተባባሪ በሚመስል መልኩ በገቢርና በዝምታ አጋዥነቱን አሳይቷል። በተለይም የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በኦርቶዶክሳውን ላይ እየተፈጸመ ያለውን ጥቃት እንዲያስቆም ሲጠየቅ ጥቃቱን ከመካድ ጀምሮ በግልጽ አጥፊዎችን እስከ መደገፍ የደረሱ ድጋፎችን ሲያደርግ ተስተውሏል፡፡ ቁጣውና ጩኸቱ ጠንከር ሲል ጥቃቱን ለማስቆም ቃል ይገባል፤ ነገር ግን ጩኸቱ በረድ ሲል የተናገረውን ሲፈጽም አይታይም፡፡ እንዲህ መሆኑ ለገዳዮች የልብ ልብ ሰጣቸው፡፡ ቤተ ክህነቱም የክርስቲያኖች ግድያና ስቃይ ደንታ የሚሰጠው አይመስልም። በየቦታው ክርስቲያኖች ሲገደሉ ምንም ካለማለት ደረጃ የደረሰው ምን ነክቶት ነው ያሰኛል፡፡ በአርሲ ዞን የተፈጸመውን ጅምላ ጭፍጨፋ በተመለከተ ኅዳር ፳፬ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም ያወጣው መግለጫም “የእንጦጦ መምህር ቢናገር በዓመት፣ ያውም እሬትን” የሚያስተርት ነው። የተሰጠው መግለጫ በሟቾቹ ከመቀለድ አይተናነስም፡፡ ችግሩን ለመንግሥትም ሆነ ለዓለም ማኅበረሰብ ለመግለጥ ካስፈለገ በሚገባ አደራጅቶ፣ ብስሉን ከጥሬ ለይቶ፣ እውነት የሆነውን ሐሰት ከሆነው አጣርቶ ነው፡፡ ይህ መግለጫ ግን ድብስብስ ያለ፣ ዓላማው የማይታወቅ ነው፡፡ ቢሆንም ግን በክርስቲያኖች ላይ እየደረሰ ያለው መከራ ማቆሚያ የሌለው፣ ለማስቆም ፍላጎት ያለው የመንግሥት አካልም የሌለ መሆኑን የሚያስገነዝብ መሆኑን መረዳት ይገባል።
በመላ ሀገሪቱ ክርስቲያኖች ተመርጠው መገደል የጀመሩት ኢሕአዴግ ደርግን አስወግዶ ሥልጣን ከያዘ ማግስት ጀምሮ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ለውጥ መጣ ከተባለበት ጊዜ ጀምሮ ግን ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ በተለይም ከሐምሌ ፳፰ ቀን ፳፻፲ ዓ.ም በጅግጅጋ የተጀመረው ክርስቲያኖችን መርጦ ማጥቃት በመቀጠልም በኦሮሚያ ክልል ምክንያት እየተፈለገ፣ ወፍ በበረረ፣ ዘንግ በተወረወረ ቁጥር ለመከራ ተዳርገዋል፡፡ የዓይናችሁ ቀለም አላማረንም፣ ሃይማኖታችሁን አልወደድነውም እየተባሉ በስቃይ ላይ ቢገኙም ችግሩን የሚፈታላቸው፣ ጩኸታቸውን የሚሰማቸው አልተገኘም፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን በአማራ ክልል ከሚሴ ዞን፣ በ፳፻፲፩ ዓ.ም ሲዳማን ራሷን የቻለች ክልል ለማድረግ መንግሥትን ጠይቀው መልስ የተነፈጋቸው የዞኑ ነውጠኞች ጥያቄውን ውድቅ ያደረጉባቸው ኦርቶዶክሳውያን የሆኑ ይመስል ከየቤታቸው እየተፈለጉ ለሞትና ለመከራ ዳረጓቸው፡፡ ሀብት ንብረታቸው ወደመ፣ ይዞታቸው እየተነጠቀ ለሌላ አካል ተሰጠ፡፡ አብያተ ክርስቲያናት ተቃጠሉ፡፡
ጥቅምት ፳፻፲፪ ዓ.ም ጅዋር መሐመድ ከመንግሥት ጋር በነበረው አለመግባባት ተከበብኩ ባለ ጊዜ ለመከራ የተዳረጉት ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ ሰኔ ፳፻፲፪ ዓ.ም የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳን መገደል ተከትሎ በክልሉ በሚኖሩ ክርስቲያኖች ላይ መውረድ የጀመረው የመከራ ዝናብ ዛሬ ድረስ አላቋረጠም፡፡ ክርስቲያኖች በክልሉ እንዳይኖሩ በሕግ ባይከለከሉም በአመፅ እና በጉልበት ከተከለከሉ ግን ዓመታት ማለፋቸው የአደባባይ ምሥጢር ከመሆን ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ በተደጋጋሚ ከመንግሥት ጋር ውይይት ተደርጎ ችግሩን እንፈታዋለን እየተባለ ቃል ቢገባም ችግሩ እየባሰበት እንጂ እየተሻለ አለመምጣቱ ቤተ ክርስቲያን የሐዘን መግለጫ ከማውጣት ያለፈ ተግባር መፈጸም እንዳለባት የሚያስገነዝብ ነው፡፡ ግን ይህ ሲሆን አይታይም።
በሰሞኑ በአርሲ ዞን የተፈጸመውን ጥቃት በተመለከተ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ባወጣው መግለጫ “በሶሌ ዲገሉ እና ጢጆ ለቡ በተባሉ ቀበሌዎች ፳፰ ኦርቶዶክሳዊያን ከየቤታቸው ተለቅመው የተገደሉ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥም ፯ቱ ሴቶችና ፳፩ ወንዶች መሆናቸው ታውቋል። በዚህ ጥቃትም እድሜያቸው ከሰባ ዓመት አዛውንት እስከ ሃያ ስምንት ቀን ጨቅላ ሕጻናት ይገኙበታል። በተመሳሳይ በዲገሉ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ፭ ኦርቶዶክሳዊያን ከመገደላቸው በተጨማሪ የሦስት ኦርቶዶክሳውያን ቤት ደግሞ ሙሉ በሙሉ ተቃጥሏል። ከዚህ ቀደም በሮቤ አንዲቶ ደብረ ምጥማቅ ማርያም ቤተ ክርስቲያን በዓለ ማርያምን አክብረው ወደ ቤታቸው በመመለስ ላይ የነበሩ ሦስት ኦርቶዶክሳዊያን ጨለማን ተገን ባደረጉ ነፍሰ ገዳዮች መገደላቸው ይታወሳል። የሀገረ ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎች ከመንግሥት የጸጥታ አካላት ጋር በተደጋጋሚና ሆን ተብሎ በሚፈጸመው የኦርቶዶክሳዊያን ጥቃት ዙሪያ በጋራ እየሠሩ የሚገኙ ሲሆን በዚህ ዐይነት የጥቃት ተግባር ላይ ተሰማርተው የሚገኙ አንዳንድ አካላት ላይ በመንግሥት በኩል የማያዳግም ርምጃ እንደተወሰደባቸው ሀገረ ስብከቱ በላከው ሪፖርት አረጋግጠዋል” በማለት ዘርዝሮታል።
ቢቢሲ አማርኛ የደረሰውን ጥቃት የዘገበው “በጥቃቱ የቤተሰብ አባላት የተገደሉባቸው በሽርካ ወረዳ፣ የጥዮ ለቡ ቀበሌ ነዋሪ፣ ኅዳር ፲፫ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም. ግድያው ሲፈጸም በአጋጣሚ በስፍራው ባለመኖራቸው እርሳቸው ቢተርፉም፣ አብዛኞቹ የቤተሰቦቻቸው አባላት እንደተገደሉባቸው ተናግረዋል። በጥቃቱ ባለቤቴ እና ልጄ፣ የአባቴ ልጆች፣ የአባቴ ሚስት፣ እኅቶቼ እና ወንድሞቼ በአጠቃላይ ሰባት ቤተሰብ ተገድለውብኛል። ከቤት ወስደው ነው የጨፈጨፏቸው” ብለዋል በመሪር ሐዘን። ቢቢሲ ባነጋገራቸው ወቅትም ከጥቃቱ የተረፉ የሁለት ዓመት እና የስምንት ዓመት ልጆቻቸውን አሳክመው እየተመለሱ እንደ ሆነ ተስፋ በቆረጠ ሁኔታ ገልጸዋል። በወረዳው ሾሌ ዲገሊቡና ቀበሌ ነዋሪ የሆኑ ሌላ ግለሰብም ባለፈው ሳምንት በተፈጸመው ጥቃት የስምንት ልጆቻው እናት የሆነችው ባለቤታቸው እና የ፲፪ ዓመት ሴት ልጃቸው እንደተገደሉባቸው ለቢቢሲ ተናግረዋል” በማለት ነው።
ከሳምንት በፊት በደራ ወረዳ በክርስቲያኖች ላይ የተፈጸመው ግድያ በልዩ ልዩ ብዙኀን መገናኛ ተዘግቦ አይተናል ሰምተናልም፡፡ እነዚህ ክርስቲያኖች በሰማዕትነት እንዲጠሩ የአምላካችን ፈቃድ ቢሆንም ከክርስቲያኖች የሚጠበቅ ተግባርና ሐላፊነት መኖሩን መዘንጋት አይገባም፡፡ እንዲህ ያለው አሰቃቂ ግድያ ሲፈጸም ጥቃቱን እንዲያስቆም መንግሥትን ከመጠየቅ ጀምሮ ሌሎች ተግባራትን ማከናወንም ይገባል፡፡ ዝም አላችሁ ላለመባል ብቻ ለግብር ይውጣ የሚሰጡ መግለጫዎች ግን ክርስቲያኖችን ተስፋ ያስቆርጣሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በአባቶች ላይ ያለው አመኔታ እንዲቀንስ ስለሚያደርግ ሊታሰብበት ይገባል፡፡ መንግሥትም ዜጎቹን ነቅቶና ተግቶ የመጠበቅ ሐላፊነቱን መወጣት ይኖርበታል፡፡

ይህ ዐይነቱ ኦርቶዶክሳውያን ላይ ያነጣጠረ ግድያ እንዲቆምና የወንጀሉ ፈጻሚዎችም ለፍርድ እንዲቀርቡ በሀገረ ስብከቱ በኩል እየተደረገ ያለው ጥረት እንደተጠበቀ ሆኖ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ጽሕፈት ቤትም በድርጊቱ እጅጉን ማዘኑን እየገለጸ ጉዳዩን ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር በመሆን የሚከታተለው መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን። በሌሎች ስፍራዎች የሚያጋጥሙ ተመሳሳይ ጥቃቶችን በእንጭጩ ለመቅጨትና ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር በመነጋገር መፍትሔ ማበጀት ይቻል ዘንድ አህጉረ ስብከት ችግሮች በሚያጋጥሙ ወቅት ሪፖርት እንዲልኩ ቀደም ሲል በደብዳቤ በተላከላቸው የስልክና ዘመናዊ የመገናኛ ዘዴዎች አማካኝነት በፍጥነት በማሳወቅ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እያሳሰብንና ለሞቱት ኦርቶዶክሳውያን ወገኖቻችን ሁሉ ልዑል እግዚአብሔር መንግሥተ ሰማያትን እንዲያወርስልን በመጸለይ የፌዴራልም ሆነ የክልል መንግሥታት የሚደርሱ ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች እንዲቆሙና መሰል ጥቃት እንዳይፈጸም ለኦርቶዶክሳዊያን ወገኖቻችን ከለላ እንዲሰጡልን እንጠይቃለን̋ ተብሎ የተነገረውን አጠናክሮ መቀጠል እንጂ በቃል እየተናገሩ ከተግባሩ መራቅ ብዙ ዋጋ ያስከፍላል።

ባይተዋርነት እስከ መቼ? ክፍል ሁለት

ባይተዋርነት እስከ መቼ? ክፍል ሁለት

ባይተዋርነት እስከ መቼ? ክፍል ሁለት

ባይተዋርነት እስከ መቼ? ክፍል ሁለት

በክፍል አንድ ጽሑፋችን ኦርቶዶክሳውያን በሀገራችን ባይተዋር ያደረጉንን ጥቂት ምክንያቶች ለማየት ሞክረናል፡፡ በዛሬው ጽሑፋችን ደግሞ ከዚህ ባይተዋርነት የመውጫ መንገዶችን ለመጠቆም እንሞክራን፡፡
1. ለሰማያዊ ክብር፣ ለዘላለማዊ ሕይወት የሚያበቃ መንፈሳዊ ዝግጅት ይኑረን፡- እንደ ቃሉ የምንኖር እምነተ ብርቱዎች እና ከምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን በአግባቡ የምንካፈል መሆን አለብን፡፡ ይህ መንፈሳዊ ዝግጅት እንደ ጥንቶቹ ጽኑ ክርስቲያኖች በአሕዛብ ፊት ያለ ፍርሃት “እኛ የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን” የምንል የዐደባባይ ምስክሮቹ እንድንሆን ያበረታናል፡፡ “ልንሔድ ከክርስቶስ ጋር ልንኖር እንናፍቃለን” ለማለት ያበቃናል፡፡ በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚፈጸመውን በደል ለመቃወም እና ፍትሕ ርትዕ ለመጠየቅ ብሎም ለማስፈን እንድንችል፣ የፍርሃትን መንፈስ ገድለን የኃይልና የሥልጣንን መንፈስ እንድንለብስ ያደርገናል፡፡ Read more

የሰላም ዋጋው ስንት ነው?

የሰላም ዋጋው ስንት ነው?

የሰላም ዋጋው ስንት ነው?

የሰላም ዋጋው ስንት ነው?

ሰላም የሚለው ቃል ሲጠራ ቀላል ቢመስልም ዋጋው ግን በገንዘብ ከመተመን በላይ ነው፡፡ ሰላም እንኳን ለሰው ልጅ ለእንስሳት፣ ለአራዊት እና በጠቅላላው ለሥነ ፍጥረት በጣም አስፈላጊ ነገር ነው፡፡ ሰላም ከሌለ ማንም ወጥቶ መግባት፣ ነግዶ ማትረፍ፣ አርሶ መብላት፣ ደግሶ መዳር አይችልም፡፡ ሠርቶ የመለወጥን ተስፋም ያመነምናል፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በጸሎተ ቅዳሴዋ “እግዚአብሔር በይቅርታው አንድ ያደርገን ዘንድ ስለ ሰላም እንማልዳለን፤ በዘመኑ ሁሉ ፍጹም ሰላምን እግዚአብሔር ይሰጣት ዘንድ እግዚአብሔርን ስለምትወድ ስለ አገራችን ኢትዮጵያ እንማልዳለን” በማለት ዕለት ዕለት ፈጣሪዋን የምታሳስበው ያለ ምክንያት አይደለም – ሰላም የሁሉ ነገር መሠረት ስለሆነ እንጂ፡፡ እንኳን ሰማያዊ ለሆነው ሃይማኖት ለምድራዊ ኑሮም ቢሆን ዓለም የምትሸልመው ሳይታክቱ ለሰላም የደከሙትን ነው፡፡ Read more

ባይተዋርነት እስከ መቼ?

ባይተዋርነት እስከ መቼ?

ባይተዋርነት እስከ መቼ?

ባይተዋርነት እስከ መቼ?

 መስከረም ፲፭ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም. በአርሲ ሀገረ ስብከት በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ ቤተ ክህነት ኦርቶዶክሳውያን ተገደሉ (ሰባት ኦርቶዶክሳውያን)፡፡ ኦርቶዶክሳውያን ጨቅላ ሕፃናትን ጨምሮ የካህናት ቤተሰብ በአሰቃቂ ሁኔታ በጥይት ተደብድበው ተገደሉ፡፡ በርካቶች ቆሰሉ፡፡
 ካህናት እና ቤተሰቦቻቸው ከቤተ ክርስቲያን እስከ ቤታቸው ታድነው ይገደላሉ፡፡
 መስከረም ፳፫ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም.) በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በአዳማ ዙሪያ ወረዳ ቤተ ክህነት በአርቱ መካነ ቅዱሳን ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች የሆኑት አባ ተክለ አብ እና ቀሲስ መሠረት ተገደሉ፡፡ በደራ፣ በወለጋ፣ በቤንሻንጉል ወዘተ
 አሮጌው ዓመት(፳፻፲፭ ዓ.ም.) በስልጤ ዞን የተለመደውን የኦርቶዶክሳውያን ደም በማፍሰስ፣ ሀብት ንብረታቸውን በማቃጠል እና በማሳደድ ነው የተሰናበተን፡፡ አዲሱ ዓመት ደግሞ የአሮጌውን ዓመት የደም ግብር መገበርን አጠናክሮ ቀጥሎበታል፡፡
 ካህኑ በዐውደ ምሕረት በአገልግሎት ላይ እያሉ በጥይት የተመቱት ጠረፍ አካባቢ በምትገኘው አጥቢያ አይደለም፡፡ እዚሁ አዲስ አበባ ነው፡፡ Read more

የአዲስ አበባ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት በ2015 ዓ.ም በ4 በ6ና በ10ኛ ክፍል ያስተማራቸውን ከ4500 በላይ ተማሪዎች አስመረቀ

ጥቅምት 04 2016 ዓ.ም (የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት)

የአዲስ አበባ ሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በ2015 ዓ.ም በ4 በ6 እና በ10ኛ ክፍል በተዘጋጀው ሥርዓተ ትምህርት ያስተማራቸውን ተማሪዎች በዛሬው ዕለት በደብረ ምጥማቅ ሰዓሊተ ምህረት ቅድስት ማርያም እና ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ካቴድራል አስመረቀ። በመርሐ ግብሩ ላይም ብጹዕ አቡነ አብርሃም የባህርዳር ሀገረስብከት ሊቀጳጳስና የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ ብጹዕ አቡነ ጴጥሮስ የሰሜን አሜሪካ የኒውዮርክ ሀገረስብከት ሊቀጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብጹዕ አቡነ ቀለሜንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከትና የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ ሊቀ ጳጳስ እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው ሊቃነ ጳጳሳት የጠቅላይ ቤተክህነት መምሪያ ኃላፊዎች የጠቅላይ ቤተክህነት የየመሪያው ኃላፊዎች ፤ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት እና የክፍለ ከተማ ቤተክህነት የየክፍሉ ኃላፊዎች የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምሪያ አመራሮች ተመራቂ ተማሪዎችና ወላጆቻቸው በተገኙበት በታላቅ ድምቀት ተከብሮ ውሏል።

የምርቃት መርሐ ግብሩ ልጅህን በሚሄድበት መንገድ ምራው በሸመገለም ጊዜ ከእርሱ ፈቀቅ አይልም በሚል መሪ ቃል የተከበረ ሲሆን በመጀመሪያ በብጹዕ አቡነ ቀለሜንጦስ መሪነት በጸሎተ ወንጌል ተከፍቷል። በመቀጠልም በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ሰብሳቢ ላዕከ ኄራን መንክር ግርማ የመግቢያ ንግግር የተደረገ ሲሆን በንግግራቸውም በአዲስ አበባ ከሚገኙ 250 አድባራት 157 የሚሆኑት በ2015 ዓ.ም ሥርዓተ ትምህርቱን መተግበራቸውንና በዛሬው ዕለት ግን 77 የሚሆኑ አድባራት በአንድ ወይም ከዚያ በላይ በሆኑ እርከኖች ተማሪዎቻቸውን ማስመዘናቸውን ገልጸዋል። በዚህም ከተፈተኑት 4500 ተማሪዎች ውስጥ 4030 የሚሆኑት ወደ ቀጣይ ክፍል መዘዋወራቸውን አብስረዋል። በ2016 ዓ.ም በ205 ደብራት 72,000 በላይ የሚሆኑ ተማሪዎች በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት እንዲማሩ እንደ እቅድ ተይዞ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

የዕለቱን ወንጌል የሰንበት ትምህርት ቤት ፍሬ የሆኑት ዲያቆን ህሊና በለጠ “እኔ የሳሮን ጽጌሬዳ የቆላም አበባ ነኝ” መኃ 2:1 በሚል ቃል መነሻነት ቃለ እግዚአብሔር አስተላልፈዋል። በመቀጠልም ብጹዕ አቡነ አብርሃም ለተመራቂ ተማሪዎችና ለወላጆች የእንኳን ደስ አላችሁ መልእክት አስተላልፈዋል። በመልዕክታቸውም “የሳንቲም ውርስ ልጆችን ያጋጫል የሃይማኖት የእውቀት የምግባር ውርስ ግን እስከ መጨረሻው ለወላጆች የሚጠቅሙ ሀገርን ሀገር የሚያሰኙ የነገዋን ቤተክርስቲያንን የሚገነቡ ተስፋዎች ያደርጋችዋል። ስለዚህም ቤተክርስቲያንን እንጠብቃት እንታዘዛት አገልግሎታችሁ ከጥቅማ ጥቅም የተነሳ ሳይሆን በነጻ የምታገለግሉበት ነውና ብዙ ጸጋና ሀብትን ይሰጣችኋል በዚህም ቤተክርስቲያናችሁ እጅግ ትደሰታለች።” ሲሉ አባታዊ ቡራኬያቸውን ሰጥተዋል።

በመጨረሻም የሽልማትና የምስጋና መርሐግብር የተካሄደ ሲሆን ከ77 አድባራት በብዙ የተማሪዎች ቁጥር ያስፈተኑንና ከተፈተኑት ውስጥ የደረጃ ተማሪዎች የነበሩትን ከብጹአን ሊቃነ ጳጳሳት እጅ የማበረታቻ ሽልማት ተሰቷቸዋል። በብጹዕ አቡነ ቀለሜንጦስ የመጨረሻ አባታዊ ቡራኬ እና መልእክት የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ሆኗል።

(የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት)

✍️YouTube 👇
https://www.youtube.com/@eotc-gssu
✍️ FaceBook 👇
https://www.facebook.com/EOTC.GSSU
✍️Telegram 👇
https://t.me/EOTCNSSU
✍️Website👇

✍️Tiktok👇

@sundayschoolunion

 

ከእግዚአብሔር ጋር መታገል

ከእግዚአብሔር ጋር መታገል

ከእግዚአብሔር ጋር መታገል

ከእግዚአብሔር ጋር መታገል

ንስሐ ገብተህ ኃጢያትን ለማስወገድ ትፈልጋለህ? አንድ ነገር አስታውስ። ኃጥያትን ለማሸነፍ የሚደረገው ትግል በሰው ጉልበት ብቻ ውጤታማ ሊሆን አይችልም። ኃጥያት ጠንካራ በመሆኗ “ወግታ የጣለቻቸው ብዙዎች ናቸው። እርሷም የገደለቻቸው ብዙዎች ናቸው” ምሳሌ(7፥26) ተብሎ ተጽፏል።

 

ይህ አዳምን፣ ሶምሶምን፣ ዳዊትና ሰለሞንን ወግቶ የጣለ ኃጢያት ያለ እግዚአሔር አጋዥነት አንተ ብቻዬን እወጣዋለው ብለህ ታስባለህ? አስቀድመህ የወደቅህበት ኃጢያት ያለ እግዚአብሔር እርዳታና ድጋፍ አንተን እንደሚቆጣጠርህ አትጠራጠር። ውጊያው ውጫዊ የሆነ ጦርነት ብቻ አይደለም። በተለይ የኃጢያት ዝንባሌ የምታሳይ ከሆነ ውጊያው እጥፍ ነው የሚሆነው። የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮ እንዲህ ይላል። “እግዚአብሔር ከተማን ካልጠበቀ ጠባቂ በከንቱ ይተጋል”(መዝሙር 127፥1)። ጌታ እራሱ “ያለ እኔ አንዳች ነገር ማድረግ አይቻላችሁም”(የሐዋ 15፥5) ይላል። እግዚአብሔርን ሳትይዝ የምታደርገው ትግል ፍጻሜው ውድቀት መሆኑን አትጠራጠር። ውጊያውን ማሸነፍ ቢቻልህ እንኳን በከንቱ ውዳሴ ተጠልፈህ መውደቅ መቻልህን አትዘንጋ። ምክንያቱም በራስህ ኃይል ታግለህ እንዳሸነፍከው ይሰማኻልና። Read more

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ

የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ሂደት ላይ ያለውን ጥያቄ በደብዳቤ አሳወቀ

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ

የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ሂደት ላይ ያለውን ጥያቄ ለአስመራጭ ኮሚቴው በደብዳቤ አሳውቋል። የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት፤ በቀኖና ቤተ ክርስቲያን አግባብ የኢጲስ ቆጶሳት ምልመላ፣ መስፈርት እና ሂደት ለሕዝብ ይፋ ሆኖ በግልፅ መከናወን እንደሚኖርበት በደብዳቤው አጽእኖት ሰጥቷል። በተጨማሪም፤ እስካሁን በተኼደበት መንገድ ከተቀጠለ፤ የሕግና የቀኖና ጥሰት፣ እንዲሁም ይሁንታ የማጣት ጉዳይ ሊከሰት እንደሚችል አሳስቧል። ደብዳቤውን የተረከቡት የአስመራጭ ኮሚቴው ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ፣ ደብዳቤውን ለኮሚቴው አቅርበው እንደሚመክሩበት አሳውቀዋል።
በሌላ በኩል፤ ከቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ እንደሚጠቁመው፤ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ በግቦት 14 ቀን 2015 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ የወሰነውን የአዳዲስ ኢጲስ ቆጶሳት ሢመት በተመለከተ በምልዓተ ጉባኤው የተሰየሙት የአስመራጭ ኮሜቴ አባላት ሥራቸውን ያጠናቀቁ መሆኑን በመግለጽ ኮሚቴው አዘጋጅቶ በሚያቀረበው እጩ ኢጲስ ቆጶሳት ምርጫ ዙርያ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ለማስተላለፍ ይቻል ዘንድ በሚል ለሰኔ 25 ቀን 2015 ዓ.ም. ምልዓተ ጉባኤ ጠርቷል። ከዚህ ጋር በተያያዘ፤ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ለአስመራጭ ኮሚቴው በደብዳቤ ያሳወቃቸው ጥያቄዎች ከተጠራው ምልዓተ ጉባኤ መስየም እና የመጨረሻ ውሳኔ በፊት ታይተው የተዛቡ አካሄዶች ይስተካከላሉ የሚል እምነት አሳድሯል።

፲፪ኛው የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ የአቋም መግለጫ

በኢ/ኦ/ተ/ቤ የሰ/ት/ቤቶች ማ/መምሪያ የዓለም አቀፍ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ፲፪ኛው ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ከግንቦት 26-27 ቀን 2015 ዓ.ም ተከናውኖ
በቀረቡ ሪፖርቶች፣ ጥናታዊ ሰነዶች፣ ከሁሉም አካባቢዎች ከቀረቡ የውይይት ግብዓቶች በመነሳት ባለ አስራ አንድ ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል።

1.  በ12ኛው ጠቅላላ ጉባኤ የቀረበውን ሪፖርትና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተቀብለን አጽድቀናል ለትግበራው በጋራ እንሰራለን፡፡
2.  ከጠቅላይ ቤተክህነት ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃና መምሪያ ሀገር አቀፍ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት እስከ አጥቢያ ሰ/ት/ቤት የቀረበውን የአደረጃጀት መዋቅር በጥልቀት ገምግመናል፡፡በጉባኤው የተሰጡ ማስተካከያዎችን በማካተት ወደ ስራ እንዲገባ ወስነናል፡፡
3.  የሥርዓተ ትምህርት መጻሕፍትን ለማሳተም የበጀት እጥረት እንዳለ ተገንዝበናል፡፡ይህንን ከቅዱስ ሲኖዶስ እስከ ሀገረ ስብከት ያሉ የቤተክርስቲያን መሪዎች በመገንዘብ ለሕትመቱ ተዘዋዋሪ በጀት/Revolving budget/ እንዲፈቀድና የተዘጋጁ መጻሕፍት ወደ ሕትመት እንዲገቡ በየደረጃው ለሚመለከታቸው አካላት ጥያቄ እንዲቀርብና ክትትል እንዲደረግ በአጽንዖት እንጠይቃለን፡፡
4.  ሀገሪቱ ላይ በሚከሰቱ የተለያዩ አለመግባባቶች ምክንያት ያለ እዳዋ እዳ የተሸከመችው ቅድስት ቤተክርስቲያናችንን በአቢያተ ክርስቲያኗ ላይ የሚደርሰው መቃጠልና መዘረፍ በምእመናን እንዲሁም በሰንበት ት/ቤት ወጣቶቻችን ላይ የሚደርስ የህይወት መጥፋት፣ የአካል መጉደልና መሳደድ እንዲቆም የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ እንጠይቃለን፡፡
5.  በተለያ ምክንያት የቤተ ክርስቲያንን መምህራንና አገልጋዮችን ማሰር እንዲቆም የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ እንጠይቃለን፡፡
6.  የቤተክርስቲያናችን አንድነት ተጠብቆ ምዕመናን ከመደናገር ወጥተው ሥርዓተ አምልኮ በነጻነት መፈጸም ይችሉ ዘንድ ይቅርታና ሰላምን ሲያስተምሩ የኖሩ የትግራይ አህጉረ ስብከት ሊቃነ ጳጳሳትና የአስተዳደር አካላት ለቤተክርስቲያ አንድነትና ለምዕመናን ሲሉ ወደ ውይይትና ይቅርታ እንዲመለሱና ቅዱስ ሲኖዶስ ያቀረበውን የሰላም ጥሪ እንዲቀበሉ በልጅነት መንፈስ እየጠየቅን ቅዱስ ሲኖዶስና በአንጻራዊ ሰላም ውስጥ ያለው የቤተ ክርስቲያን መዋቅር በትግራይ በተፈጠረው ጦርነት ለተፈጠረው ችግር ተገቢውን ድጋፍ ትኩረት ሰጥቶ እንዲሰራ እንጠይቃለን፡፡
7.  በቃለ አዋዲ የተደነገገው የሰበካ አስተዳደር ጉባኤ አደረጃጀት ከአጥቢያ ቤተክርስቲያን በቀር እየተተገበረ አለመሆኑ በቤተክርስቲያን አስተዳደራዊ ሂደት ላይ ክፍተት እንደፈጠረ በጉባኤው በጥልቀት ተነስቷል፡፡ስለሆነም ከወረዳ ቤተክህነት እስከ ጠቅላይ ቤተክህነት ድረስ በቃለ አዋዲው መሰረት የካህናት፣የምዕመናን እና የሰንበት ት/ቤት አባላት ተሳትፎ እንዲከበር በታላቅ አጽንዖት እንጠይቃለን፡፡
8.  ሥርዓተ አምልኮ ለመፈጸም፣ልጆች ወልዶ ለማሳደግና ተተኪ ትውልድ ለማፍራት ሀገር ያስፈልጋል፡፡በሀገር ውስጥም ሰላም ከሌለ ምንም ማከናወን አይቻልምና በመላው ሀገሪቱ በተቃርኖ የሚገኙ አካላት በሚያርጉት ጦርነትና የእርስ በእርስ ግጭት ምክንያት ንጹሀን ዜጎች ሕጻናት፣ሴቶችና ካህናት ላይ የሚደርስ እንግልትና ጉዳት እየከፋ መምጣቱን በመገንዘብ ልዩነታቸውን በውይይትና በድርድር ብቻ እንዲፈቱ እንጠይቃለን፡፡
9.  ከሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ ችግሮች በፍጹም ቅድስት ቤተክርስቲያናችንን የሚመጥኑ ሆነው አላገኘናቸውም፡፡በመሆኑም ሲመቱ ሕገ ቤተክርስቲያንን፣ፍትሐነገሥትንና ቃለ አዋዲን ባከበረና ባከበረ መልኩ ብቻ እንዲደረግ በልጅነት መንፈስ እንጠይቃለን፡፡
10.  በቤተክርስቲያናችን የሚስተዋሉ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት በተለያዩ የቤተ ክርስቲያን አካላት ተጠንተው የሚቀርቡ የመፍትሔ ሀሳቦችን ቅዱስ ሲኖዶስ በምክረ ሃሳብነት እንዲቀበላቸውና በማዳበር እንዲተገበሩ አቅጣጫ እንዲሰጥ ከጠቅላይ ቤተክህነት ጀምሮ ያሉ የቤተ ክርስቲያን መዋቅር አካላት የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ ያለምንም መሸራረፍ ተግባራዊ እንዲያደርግ በአጽንዖት እናሳስባለን፡፡
11.  በቤተክርስቲያናችን ውስጥ የሚስተዋሉ የአስተዳደር ችግሮች እንዲፈቱ በሚያስችሉ ሥራዎች ላይ ሁሉ በመሳተፍና እንደ ቤተክርስቲያን ተተኪ ልጅነታችን የበኩላችንን ኃላፊነት በባለቤትነት መንፈስ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት እስከ አጥቢያ ባለዉ መዋቅር ትኩረት ሰጥተን የምንሠራ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

ግንቦት 27 ቀን 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ

የቅዱስ ፓትርያርኩ የግንቦት ፳፻፲፭ ዓ.ም ርክበ ካህናት ጉባኤ መክፈቻ ንግግር

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ፣

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና በሰሜን አሜሪካ የኒዮርክ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ፣

ብፁዕ አቡነ ሔኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ

ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፣ Read more

ቤተ ክርስቲያን የአንድ አካል ብቻ አይደለችም፤ የካህናት፣የምእመናን እና የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ጭምር እንጂ!

ከሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የተላለፈ ወቅታዊ መልእክት

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ዋና ተግባሩ የሆነውን ሐዋርያዊ ተልእኮ በትጋት እና በስፋት ከማስፈጸም ይቅል በሥጋ ሐሳብ ተቀፍድዶ ጥንታዊቷን እና አማናዊቷን ቤተ ክርስቲያን በማይመጥን ደረጃ ላይ መገኘቱን የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ተገንዝቧል። በተለይ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን፣ አደረጃጀቱን ለማዘመን እና የሥራ አፈጻጸም ስልትን ከዘመኑ ጋር ለማጣጣም እንዲያስችል በተለየዩ ጊዜያት በባለሙያዎች ተጠንተው የተዘጋጁ መፍትሔ አመላካች ሰነዶች ልዩ ልዩ ምክንያት እየተለጠፈባቸው ተገፍተው መወገዳቸውን ታዝበናል። ስለሆነም አስተዳደራዊ ክፍተቱ በከፍተኛ ደረጃ የወለደው ችግር የአደባባይ ምሥጢር ሆኖ ተገልጧል:: Read more