ይቅርታና ክረምት

ይቅርታና ክረምት

ይቅርታና ክረምት

ይቅርታና ክረምት

በወርሐ ክረምት ከሚታሰቡ እና ከሚናፈቁ ነገሮች አንዱ አዲሱን ዓመት መቀበል፣ ስለ አዲሱ ዓመት ማሰብ ፣አዲስ ተስፋ፣ አዲስ ምኞትና በአዲሱ ዓመት ስለ ሚሠሩ ሥራዎች፣ ስለምናሳካቸው ተግባራት እቅድ ማቀድ ነው።

አብዛኞቻችን ከማናስበው ነገር አንዱ አሮጌውንስ ዓመት እንዴት እንሸኘው የሚለውን ነው:: ሁሌም ይሄ ሲታሰብ ወደ አእምሮ ከሚመጡ ነገሮች ዉስጥ ጾመ ፍልሠታ አንዱ ነው። በተለይም ደግሞ ከአዲስ ዓመት በፊት መምጣቱ አሮጌውን ዓመት ለመሸኘት ጥሩ አጋጣሚ ነው። በፍልሰታ ሁሉም ኦርቶዶክሳዊ ምዕመን በመሚባል ደረጃ ከሕፃን እስከ አዋቂ የሚጾምበት የሚያስቀድስበት ወቅት ነው። ግን ምን ያህሎቻችን ነን ቅዳሴ ስንሄድ የካህኑን “በልቦናው ቂምን ያዘለ ክፋትን ያሰበ ቢኖር እዚህ አይቁም” የሚለውን ቃል ልብ የምንል የሚለው ሌላ ጥያቄ ነው።

ጾም ጸሎታችን ቅዳሴያችን ምጽዎታችን ሳይቀር ያለ ይቅርታ በረከት ማናገኝበት እንደሆነ የምናስበው። ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ (ለስም አጠራሩ ክብር ይግባውና) በማቴ 5÷23-24 ባለው ኃይለ ቃል፤ “እንግዲህ መባህን በመሰዊያው ላይ ብታቀርብ፣ በዚያም ወንድምህ አንዳች አንተ ላይ እንዳለው ብታስብ፣ በዚያ በመሰዊያው ፊት መባህን ትተህ ሂድ፤ አስቀድመክም ከወንድምክ ጋር ታረቅ፤ በኋላም መጥተክ መባክን አቅርብ።” ያለውን አምላካዊ ቃል አስበን አሮጌው ዓመታችንን በይቅርታ ለመሸኘት የተዘጋጀን መሆን ይገባናል። በዘዉትር ጸሎት ላይ፤ “በደላችንን ይቅር በለን፣ እኛም የበደሉንን ይቅር እንደምንል” እንላለን። ታድያ፤ ይቅርታ ምንድነው? ለምንስ ነው ይቅርታ ማደርገው? ደሞስ ለማ? የሉትን ጥያቄዎች በመመለስ አሮጌውን ዓመታችንን በይቅርታ ለመሸኘት እንዘጋጅ።

ቅዱስ ሲኖዶስ ዘጠኝ ኢጲስ ቆጶሳትን መረጠ

ቅዱስ ሲኖዶስ ዘጠኝ ኢጲስ ቆጶሳትን መረጠ

ቅዱስ ሲኖዶስ ዘጠኝ ኢጲስ ቆጶሳትን መረጠ

ቅዱስ ሲኖዶስ ዘጠኝ ኢጲስ ቆጶሳትን መረጠ

ቅዱስ ሲኖዶስ ዘጠኝ ኢጲስ ቆጶሳትን መረጠ

ቅዱስ ሲኖዶስ ዘጠኝ ኢጲስ ቆጶሳትን መረጠ
—-
የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ፤ ዛሬ ረቡዕ፣ ሰኔ 28 ቀን 2015 ዓ.ም. በአካሄደው ልዩ ስብሰባ ዘጠኝ ኢጲስ ቆጶሳትን መርጧል።

ዛሬ የተመረጡት ኢጲስ ቆጶሳት በኦሮሚያ እና በደቡብ ክልሎች፤ ተደርበው በቆዩ፣ ክፍት በሆኑ እና አንገብጋቢ ተብለው በግንቦት 2015 ዓ.ም. በነበረው የርክበ ካህናት መደበኛ ጉባኤ ስብሰባ ላይ በተለዩትና ሰባት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ያሉበት አስመራጭ ኮሚቴ በተሰየመላቸው መሠረት ነው።

ኢጲስ ቆጶሳቱ የተመረጡላቸው ሀግረ ስብከቶች ሰባቱ በኦሮሚያ ክልል የሚገኙ ሲሆን ሁለቱ በደቡብ ኢትዮጵያ የሚገኙ ናቸው። ከይፋዊው የቅዱስ ሲኖዶስ መግለጫ ላይ ባገኘነው መረጃ መሠረት ዝርዝራቸ፦

ለኦሮሚያ ክልል ሰባት አህጉረ ስብከት፤
1. አባ ሣህለ ማርያም ቶላ – ምዕራብ አርሲ – ሻሸመኔ ሀገረ ስብከት
2. አባ ወልደ ገብርኤል አበበ – ምሥራቅ ወለጋ ሀገረ ስብከት
3. አባ ጥላሁን ወርቁ – ምሥራቅ ሐረርጌ ሀገረ ስብከት
4. አባ ዓምደ ሚካኤል ኀይሌ – ሆሮ ጉድሩ ወለጋ – ሻምቡ ሀገረ ስብከት
5. አባ ኀይለ ማርያም ጌታቸው – ድሬዳዋ ሀገረ ስብከት
6. አባ ተክለ ሃይማኖት ገብሬ – ምዕራብ ወለጋ ሀገረ ስብከት
7. አባ እስጢፋኖስ ገብሬ – ቡኖ በደሌ ሀገረ ስብከት

ለደቡብ ኢትዮጵያ ሁለት አህጉረ ስብከት፤
8. አባ ክፍለ ገብርኤል ተክለ ሐዋርያት – ጌድኦ አማሮ እና ቡርጂ ልዩ ወረዳዎች ሀገረ ስብከት
9. አባ ስብሐት ለአብ ወልደ ማርያም – ዳውሮ እና ኮንታ ሀገረ ስብከት ናቸው።

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ

የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ሂደት ላይ ያለውን ጥያቄ በደብዳቤ አሳወቀ

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ

ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ

የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ሂደት ላይ ያለውን ጥያቄ ለአስመራጭ ኮሚቴው በደብዳቤ አሳውቋል። የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት፤ በቀኖና ቤተ ክርስቲያን አግባብ የኢጲስ ቆጶሳት ምልመላ፣ መስፈርት እና ሂደት ለሕዝብ ይፋ ሆኖ በግልፅ መከናወን እንደሚኖርበት በደብዳቤው አጽእኖት ሰጥቷል። በተጨማሪም፤ እስካሁን በተኼደበት መንገድ ከተቀጠለ፤ የሕግና የቀኖና ጥሰት፣ እንዲሁም ይሁንታ የማጣት ጉዳይ ሊከሰት እንደሚችል አሳስቧል። ደብዳቤውን የተረከቡት የአስመራጭ ኮሚቴው ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስ፣ ደብዳቤውን ለኮሚቴው አቅርበው እንደሚመክሩበት አሳውቀዋል።
በሌላ በኩል፤ ከቅዱስ ሲኖዶስ ጽሕፈት ቤት የተገኘው መረጃ እንደሚጠቁመው፤ የቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባዔ በግቦት 14 ቀን 2015 ዓ.ም ባደረገው ስብሰባ የወሰነውን የአዳዲስ ኢጲስ ቆጶሳት ሢመት በተመለከተ በምልዓተ ጉባኤው የተሰየሙት የአስመራጭ ኮሜቴ አባላት ሥራቸውን ያጠናቀቁ መሆኑን በመግለጽ ኮሚቴው አዘጋጅቶ በሚያቀረበው እጩ ኢጲስ ቆጶሳት ምርጫ ዙርያ ተወያይቶ ውሳኔዎችን ለማስተላለፍ ይቻል ዘንድ በሚል ለሰኔ 25 ቀን 2015 ዓ.ም. ምልዓተ ጉባኤ ጠርቷል። ከዚህ ጋር በተያያዘ፤ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ለአስመራጭ ኮሚቴው በደብዳቤ ያሳወቃቸው ጥያቄዎች ከተጠራው ምልዓተ ጉባኤ መስየም እና የመጨረሻ ውሳኔ በፊት ታይተው የተዛቡ አካሄዶች ይስተካከላሉ የሚል እምነት አሳድሯል።

በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የሚገኙ የሰንበት ትምህርት ቤቶች የማጠቃለያ ፈተና  ተሰጠ

በሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሥር በሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በሀገረ ስብከቱ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት አስተባባሪነት አዲሱን ሥርዓተ ትምህርት ተግባራዊ ባደረጉ ሰ/ት/ቤቶች ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲካሄድ የቆየው ማጠቃለያ ፈተና በዛሬው ዕለት በተሳካ ሁኔታ ተጠናቋል።

በሀገረ ስብከት ደረጃ 2014 ዓ.ም የአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት ማጠቃለያ በደመቀ ሁኔታ በደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ትምህርት ቤት ጊዜያዊ የመሰብሰቢያ አዳራሽ መሰጠቱንም ነው የተገለጸው።

በፈተና ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ቤተ ክርስቲያን አስተዳዳሪ ንቡረ ዕድ ቆሞስ አባ መዘምር አሰግደው ፣የሀገረ ስብከቱ ሰንበት ት/ቤት ማደራጃ ክፍል ሓላፊ መጋቤ ሃይማኖት ቀሲስ አብርሃም ሙሉጌታ እንዲሁም የሀገረ ስብከቱ ትምህርት ክፍል ሓላፊ ሊቀ አዕላፍ ቀሲስ ዮርዳኖስ አቢ በተገኙበት በተሳካ ሁኔታ መካሄዱን ከሀገረ ስብከቱ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ይፋዊ ፌስቡክ ገጽ ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።

50 ሺህ መጻሕፍት ለ50 ሰንበት ት/ቤቶች

የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት የሰንበት ትምህርት ቤት ማደራጃ ክፍል በጦርነት ወቅት ጉዳት ለደረሰባቸው በ10 ወረዳ ውስጥ ለሚገኙ ሰንበት ትምህርት ቤቶች 50 ሺህ መጻሕፍት ለማበርከት ድጋፍ ማሰባሰብ መጀመሩን አስታውቋል።

ድጋፉ የሚደረገው በወቅታዊ ጦርነት ምክንያት ጉዳት ለደረሰባቸው በ10 ወረዳ ቤተ ክህነቶች ሥር ለሚገኙ ሃምሳ ሰንበት ትምህርት ቤቶች 50 ቤተመጻሕፍት ለመክፈት በአንድ ወር ጊዜ ውስጥ 50 ሺህ መጻሕፍት ድጋፍ ለማድረግ ቅድመ ዝግጅት መደረጉ ተመላክቷል።

ሁሉንም ምዕመናንን ተሳታፊ ያደረገ የልገሳ መርሐ-ግብር ከየካቲት 13 ቀን 2014 ዓ.ም ጀምሮ ለ1 ወር የሚቆይ መጻሕፍት የማሰባሰብ ተግባር መጀመሩን የሀገረ ስብከቱ ሰንበት ትምህርት ቤት ማደራጃ ክፍል ተቀዳሚ ምክትል ሊቀ መንበር ዲያቆን ስንታዬሁ ማሩ አስታውቀዋል።

የመጻሕፍት ልገሳ ማሰባሰብ መርሐ-ግብሩ በተመረጡ አድባራትና የሚካሄድ ሲሆን የመጻሕፍት ልገሳ ተግብሩ ከአንድ ወር በኋላ ሲጠናቀቅ ከየሰንበት ትምህርት ቤቱ በተውጣጡ ተወካዮች አማካኝነት በተመሳሳይ ቀን በ10ሩም ወረዳዎች ርዕሰ ከተሞች ድጋፍ ይደረጋል ብለዋል።

የመጻሕፍት ስጦታው የእርስ በእርስ የመደጋገፍ ግንኙነታችንን ለማጠንከርና በጦርነቱ ውስጥ የነበሩ ሰንበት ትምህርት ቤቶቻችንን በተሻለ መልኩ ለማጠናከር የስርጭት ተግባራት ይከናወናል ሲሉ ዲያቆን ስንታየሁ ተናግረዋል።

መንፈሳዊ በዓል ለማክበር በወጡ ኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚደርስ ጥቃትን አጥብቀን እንቃወማለን

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በአደባባይ ከምታከብራቸው በዓላት መካከል አንዱ የሆነውን የጥምቀት በዓል እና የቃና ዘገሊላ በዓልን በመላ ሃገሪቱ በሚባል ደረጃ በሠላም ለማክበር የተቻለ ሲሆን ለዚህ ደግሞ ቤተክርስቲያኒቱ እና አማኞቿ በጋራ ላሳዩት ኦርቶዶክሳዊ ሥነ ስርዓትና ለጸጥታ ኃይሉ ባሳዩት መልካም ትብብር ሊመሰገኑ ይገባቸዋል።
ጥር 12 ቀን 2014 ዓ.ም በየሺ ደበሌ አካባቢ በምትገኘው የወይብላ ማርያም ታቦትን አክብረው በሚጓዙ ካህናት ፣ የሰንበት ት/ቤት ወጣቶች እና አዛውንት፣ ጎልማሳና ወጣት ምዕመናን ላይ ለጸጥታ ማስከበር ስራ በተሰማራ የጸጥታ አካል ኃይል የተሞላበት ጥቃት ምክንያት የደረሰው ችግር በተደጋጋሚ አንድ አካባቢ ሆነ ተብሎ ሃይማኖታዊ ሥርዓታቸውን የሚፈጽሙ ክርስቲያኖችን ከማወክ አልፎ ለሞት መዳረጉ በቤተክርስቲያናችን ላይ የሚደርሰውን በደል የሚያሳይ ኢ፟-ሰብአዊ እና ኢ-ፍትሃዊ ድርጊት በመሆኑ የሰንበት ት/ ቤቶች አንድነት በጽኑ ይቃወማል።
ተመሳሳይ ድርጊት ባለፈው ዓመትም የተከናወነ በመሆኑ ካለፈው ተመክሮ በመነሳት ከሚመለከታቸው የቤተ ክርስቲያን እና የጸጥታ አካላት ጋር በዓሉ በሰላም ለማክበር ሰፊ ውይይት በማድረግ ሁሉም ድርሻውን ለመወጣት ኃላፊነት ተወስዶ  በዚያ መልኩ እንዲፈጸም ተደርጓል። ነገር ግን ችግሩ በቦታው ዘንድሮም በድጋሚ መፈጠሩ በአጋጣሚ የተፈጠረ ክስተት ሳይሆን የመንግስትን ስልጣን ተጠቅመው ቤተ ክርስቲያኒቱን የሚያጠቁ አካላት ለመኖራቸው ትልቅ ማሳያ በመሆኑ መንግስት አስቸኳይ ማስተካከያ እርምጃ እንዲወስድ፣ እንዲሁም በድርጊቱ በቀጥታ የተሳተፉና ትዕዛዝ በመስጠት ያስፈጸሙ አካላትን በሕግ አግባብ እንዲጠየቁና ውጤቱን ለህዝቡ ይፋ እንዲያደርግ እያሳሰብን፣በዚህ ሂደት ለተፈጠረው ችግር የተሰማንን ጥልቅ ሀዘን እየገለጽን በቀጣይ ሙሉ ሂደቱን እና ቀጣይ ሥራዎችን የምናሳውቅ መሆኑን እንገልጻለን።
እግዚአብሔር ኢትዮጵያን ይባርክ!!!
የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት
ጥር 13 ቀን 2014 ዓ.ም