የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት - በኢ/ኦ/ተ/ቤ የመንበረ ፓትርያርክ ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ አንድነቱ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ተቋማዊ ራእይ፣ ተልእኮ
      • መዋቅራዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቋማዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማስፈጸሚያ
    • ስልታዊ እቅድ 2018 – 2021 ዓ/ም
  • ሥርዓተ ትምህርት
    • መሠረታዊ መረጃዎች
    • የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት አደረጃጀት መመሪያ
    • የሥርዓተ ትምህርቱ መመማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
    • የሥርዓተ ትምህርቱ ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ /ካሌንደር
    • የመምህራን ሥልጠና እና መልእክቶች
    • መጻሕፍቱን ለማግኘት እና ተጨማሪ መረጃ
    • ልዩ ልዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች
  • ፕሮጀክቶች
  • መዝሙረ ማኅሌት
    • የመስከረም ወር መዝሙሮች
      • የዮሐንስ መዝሙር
      • የመስቀል መዝሙሮች
      • የብዙኃን ማርያም መዝሙር (መስከረም ፳፩ )
      • የዘመነ ጽጌ መዝሙር
    • የጥቅምት ወር መዝሙሮች
      • የአብርሃ ወአጽብሐ መዝሙር (ጥቅምት 4 ቀን)
    • የኅዳር ወር መዝሙሮች
      • የቅዱስ ሚካኤል መዝሙር (ኅዳር 12 ቀን)
    • የጥር ወር መዝሙሮች
      • የዘመነ ጥምቀት መዝሙር
      • የቃና ዘገሊላ መዝሙር (ጥር 12 ቀን)
    • የመጋቢት ወር መዝሙሮች
      • የወርኃ ጾም መዝሙሮች
      • የሆሣዕና መዝሙራት
      • የሰሙነ ሕማማት መዝሙሮች
  • ዜና
    • አጫጭር ዜናዎች
    • ዝርዝር ዜናዎች
    • ወቅታዊ መረጃዎች
    • ማስታወቂያ
      • የሰንበት ትምህርት ቤቶች መጻሕፍት እንግሊዝኛ ትርጉም ሥራ ተሳትፎ ጥሪ
  • ያግኙን
  • ቋንቋ
    • ትግርኛ
    • Afaanoromo
  • Menu Menu

መዝሙር 359 - ተቀነዩ ለእግዚአብሔር

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/1.-ተቀነዩ-ለእግዚአብሔር.mp3

ተቀነዩ ለእግዚአብሔር በፍርሐት
ምሕረቱ ለዘላለም ነውና/2/
ጾምን እንጹም ሰውንም እናፍቅር
አዝ . . .
ሰንበትን እናክብር ጽድቅንም እንፈጽም
አዝ . . .
ከእህል ብቻ አይደለም ጾምን መጾም
ክፉ ከመናገር መከልከል ይቅደም
አዝ . . .
ፈተናውስ ለርሱ ለጌታችን አልቀረም
አዝ . . .
ምሳሌውን ከርሱ ከጌታችን እንውሰድ
አዝ . . .

መዝሙር 360 - ገዳመ ቆሮንቶስ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/2.-ገዳመ-ቆሮንጦስ.mp3

ገዳመ ቆሮንቶስ የትምህርት ገበታ
ባንቺ ተፈተነ መምህርና ጌታ
አርባ መዓልትና አርባ ሌሊት ጹመህ
ሦስትን ጥያቄዎች ፈታኝ ቢያቀርብብህ
በፍጹም ትሕትና ታግሠህ ታግሠህ
ለኛ አርአያ ልትሆን ፈተና ተቀበልህ
አዝ . . .
ጌታ ሆይ ፈታኝህ አንተ ያሳፈርኸው
ይከታተላል ዛሬም ጠላታችን ነው
በረቂቅ ጥበብህ በማንመረምረው
ድል አድራጊው ጌታ እባክህ ድል ንሣው
ይኽ ክፉ መንፈስ የማይታይ ጎልቶ
ትዕቢትና ስስት መርዝ ሆኖ ገብቶ
ሊፈጀን ነውና እርስ በርስ አጣልቶ
ጌታ ሆይ አሳየን ዝክረ ስሙ ጠፍቶ
አዝ . . .
ሰው በእንጀራ ብቻ ሊኖር እንደማይችል
ለመጣብህ ፈታኝ በግልጽ አውጀሃል
ኃይል ስለሌለን በምንበላው እህል
አቤቱ አይለየን ዘወትር ያንተ ቃል
አዝ . . .
(መዝሙረ ሐዋዝ)

መዝሙር 361 - የነፍሳችን ቤዛ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/3.-የነፍሳችን-ቤዛ.mp3

         (አማን በአማን በሚለው ዜማ)
የነፍሳችን ቤዛ የቅዱሳን ሀብት (2)
ጸጋን የሚያሰጠን ጾም ነው መድኃኒት (2)
የእስራኤል ልጆች በሙሴ ሲመሩ (2)
በፍጹም ጸሎት ባሕሩን ተሻገሩ (2)
ቅዱሳን አባቶች ጾም ነው ጋሻቸው(2)
ወደ ሕይወት መንገድ የሚመራቸው (2)
ክፍላችን እንዲሆን ከቅዱሳን ጋራ (2)
ፍቅር ቤታችንን በጸሎት እንስራ(2)
ልባችንም ይሁን የጸሎት ጎዳና(2)
የእግዚአብሔር መንግሥት እድንወርስ በጤና (2)

መዝሙር 362 - ፍቅርና ሰላምን

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/4.-ፍቅርና-ሰላምን.mp3

        (በጌቴ ሴማኔ በሚለው ዜማ)
ፍቅርና ሰላምን ታፈራለች ጾም
ፍጻሜ የሌለው እስከ ዘለአለም
የጾምንም ፍሬ ሁላችን ዐውቀን
ለጸሎት እንትጋ ፍሬዋ አይለፈን
አምላክ ተፈተነ በክፉ ጠላት
ጾምን ሲመሠርት ስለኛ ሕይወት
አምላክ ተሸከመ ሕመማችንን
የሕይወትን ውሃ ከጎኑ ሰጠን
ሕዝቦችህን ጠብቅ ከክፉ ፈተና
ቅዱስ አምላካችን ኃይላችን ነህና
(መዝሙረ ስብሐት)

መዝሙር 363 - ጾም ታድናለች

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/5.-ጾም-ታድናለች.mp3

            (የአብርሃም አምላክ በሚለው ዜማ)
ነቢዩ ዳንኤል በጾም ስላመነ
ከአንበሶች ጒድጓድ ሕይወቱን አዳነ
ኤልያስ የወጣ በእሳት ሠረገላ
በጾም በጸሎት ነው አይደለም በሌላ
የነፍስን ቍስል ጾም ታድናለች
የሥጋን ፍላጎት እያደከመች
እስቲ ልብ እናድርግ እናስተውል ደግሞ
ጌታ ለሐዋርያት ያላቸውን ቀድሞ
ይህ ርኩስ መንፈስ ሊወጣ የሚችል
በጾም በጸሎት ነው እንደ ወንጌሉ ቃል
(መዝሙረ ስብሐት)

መዝሙር 364 - መመኪያዬ አንተ ነህ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/6.-መመኪያዬ-አንተ-ነህ.mp3

መመኪያዬ አንተ ነህ የነፍሴ መዳኛ/2/
ተመልከት ወይኔ አትስጠኝ ለዳኛ
ሕይወቴን ላንተ/2/ ብያለሁ
አምላክ የኔ ጌታ የት አገኝሃለሁ
ከበደሌም አንጻኝ ደግሞም ከኃጢአቴ/2/
በመንፈስ ይቀደስ መላው ሰውነቴ
አዝ . . .
ዐቀበቱ ልቤ በጭንጫው ትዕቢት/2/
አሸብርቆ ነበር አይፈርስ መስሎት
አዝ . . .
የጾም ንጉሥ መምጣት ስለተነገረ/2/
መደልደል አለበት እየተሰበረ
አዝ . . .
ሶስናን ያዳንካት ከሐሰት ምስክር/2/
እኔንም አድነኝ ካልታሰበ ነገር
(መዝሙረ ስብሐት)

መዝሙር 365 - ለጾም እናድላ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/7.-ለጾም-እናድላ.mp3

          (ሰብሕዎ በጸናጽል በሚለው ዜማ)
ለጾም እናድላ በአንድነት ሆነን
ዋጋችን በሰማይ እንዲከፈለን
በንጹሕ እንምራ ሕይወታችንን
የገነት በር እንዳይጠፋብን
በንስሓ እናንጻት ነፍሳችንን
ትዕዛዙን እንጠብቅ የአምላካችንን

መዝሙር 366 - በጾም ወበጸሎት

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/8.-በጾም-ወበጸሎት.mp3

ሃሌ ሃሌ ሉያ በጾም ወበጸሎት (2)
ተመጠወ ሙሴ ኦሪተ አሥሮነ ቃላት (2)
ሃሌ ሃሌ ሉያ በጾም እና በጸሎት (2)
ተቀበለ ሙሴ ኦሪትን(ጽላትን) አሥርቱ ቃላትን(2)
(ቅዱስ ያሬድ)

መዝሙር 367 - ክርስቶስኒ ጾመ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/9.-ክርስቶስኒ-ጾመ.mp3

ክርስቶስኒ ጾመ
በእንቲአነ መድኃኒነ ጾመ
አርአያ ዚአሁ ከመ የሀበነ/2/
(ቅዱስ ያሬድ)

መዝሙር 368 - ይጹም ልሳን (በቁም ዜማ)

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/10.-ይጹም-ልሳን.mp3

ይጹም ዓይን፣ ይጹም ልሳን

እዝንኒ ይጹም እምሰሚዓ ሕሱም

በተፋቅሮ ወበሰላም

         ዐይን ይጹም፣ አንደበትም ይጹም

        ጆሮም ይጹም ክፉ ከመስማት

        በፍቅር እና በሰላም

                    (ቅዱስ ያሬድ)

መዝሙር 369 - ዘጾመ ወጸለየ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/11.-ዘጾመ-ወጸለየ.mp3

ዘጾመ ወጸለየ ወሰአለ (2)
እሙነ ይነስእ ዕሴቶ (2)
የጾመ የጸለየ የለመነ (2)
እውነት ነው ዋጋውን ይቀበላል (2)
(ቅዱስ ያሬድ)

Search Search

Recent Posts

  • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ
  • ሦስተኛ ዙር የ፲፪ ክፍል ምርቃት መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት ተከናወነ።

Archives

  • April 2026
  • September 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • May 2025
  • April 2025
  • October 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • July 2022
  • June 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
© Ethiopian Orthodox Church Global Sunday School Union | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
  • Link to Youtube
  • Link to Telegram
  • Link to TikTok
Link to: የቅዱስ ፓትርያርኩ የዐቢይ ፆም መልዕክት Link to: የቅዱስ ፓትርያርኩ የዐቢይ ፆም መልዕክት የቅዱስ ፓትርያርኩ የዐቢይ ፆም መልዕክት Link to: የሆሣዕና መዝሙራት Link to: የሆሣዕና መዝሙራት የሆሣዕና መዝሙራት
Scroll to top Scroll to top Scroll to top