ዕርገተ ክርስቶስ

“እያዩት ከፍ ከፍ አለ፤ ደመናም ከዓይናቸው ሰውራ ተቀበለችው” ሐዋ. 1÷9

ዕርገት ማለት ወደላይ ከፍ ከፍ ማለት ሲሆን የመሬትን የስበት ኃይል የሚያሸንፍ ከፍታ ነው፡፡ ክርስቶስ ወደ ሰማይ ያረገው የመሬት የስበት ኃይልሳይገድበው ነው፡፡ የክርስቶስ ዕርገት ቀድሞ በትንቢት የተነገረ፤ በሚያምኑት ዘንድ በናፍቆት ሲጠበቅ የቆየ እና በራሱ በጌታችን የተሰበከ ነው፡፡

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለ፴፫ ዓመታት ከሦስት ወራት በምድር ኖሯል፡፡ በ፴ ዓመቱ ተጠመቀ ለ፫ ዓመታት አስተማረ፣ ስለ ኃጢአታችን በመስቀል ላይ ቤዛ ሆነልን፡፡ በሦስተኛውም ቀን ከሙታንተለይቶ ተነሣ፤ ለደቀ መዛሙርቱም ተገለጠላቸው፡፡ Read more

ቤተ ክርስትያን እና አመራሮቿ

ቤተ ክርስቲያን በምን ዓይነት የአመራር ሁኔታ ውስጥ ትገኛለች?

አመራር ሲባል የአንድን አካል እሴት፣ እምነት፣ በጎ አስተሳሰብና ጠባይ በተመሪዎች ውስጥ በማሳደር አርአያ በሚሆን አግባብ በጎ ተጽእኖ ማሳረፍ ማለት ነው። ወደ ቤተ ክርስቲያን በቀረበ መልኩ ሲተረጎም ደግሞ መልካም አርአያነት ባለው ሕይወትና በዕውቀት ምእመናን መመገብና ለሰማያዊ ሕይወት ማብቃት ማለት ነው። የሚያሠራና ተደራሽ መዋቅር መዘርጋት፣ አቅም ያለው የሰው ኃይል ማፍራት፣ አገልጋይና አገልግሎትን ማገናኘት፣ የተማከለ የፋይናንስ ሥርዓት መዘርጋት፣ አሳታፊነት እና ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ተባብሮ መሥራት የመልካም አመራር መገለጫዎች ናቸው። Read more

የቅዱስ ፓትርያርኩ የግንቦት ፳፻፲፭ ዓ.ም ርክበ ካህናት ጉባኤ መክፈቻ ንግግር

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!

ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተ ክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ እና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ፣

ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ እና በሰሜን አሜሪካ የኒዮርክ እና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ፣

ብፁዕ አቡነ ሔኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ

ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፣ Read more

ቤተ ክርስቲያን የአንድ አካል ብቻ አይደለችም፤ የካህናት፣የምእመናን እና የሰንበት ትምህርት ቤት አባላት ጭምር እንጂ!

ከሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት የተላለፈ ወቅታዊ መልእክት

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ዋና ተግባሩ የሆነውን ሐዋርያዊ ተልእኮ በትጋት እና በስፋት ከማስፈጸም ይቅል በሥጋ ሐሳብ ተቀፍድዶ ጥንታዊቷን እና አማናዊቷን ቤተ ክርስቲያን በማይመጥን ደረጃ ላይ መገኘቱን የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት ተገንዝቧል። በተለይ መልካም አስተዳደርን ለማስፈን፣ አደረጃጀቱን ለማዘመን እና የሥራ አፈጻጸም ስልትን ከዘመኑ ጋር ለማጣጣም እንዲያስችል በተለየዩ ጊዜያት በባለሙያዎች ተጠንተው የተዘጋጁ መፍትሔ አመላካች ሰነዶች ልዩ ልዩ ምክንያት እየተለጠፈባቸው ተገፍተው መወገዳቸውን ታዝበናል። ስለሆነም አስተዳደራዊ ክፍተቱ በከፍተኛ ደረጃ የወለደው ችግር የአደባባይ ምሥጢር ሆኖ ተገልጧል:: Read more