የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት - በኢ/ኦ/ተ/ቤ የመንበረ ፓትርያርክ ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ አንድነቱ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ተቋማዊ ራእይ፣ ተልእኮ
      • መዋቅራዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቋማዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማስፈጸሚያ
    • ስልታዊ እቅድ 2018 – 2021 ዓ/ም
  • ሥርዓተ ትምህርት
    • መሠረታዊ መረጃዎች
    • የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት አደረጃጀት መመሪያ
    • የሥርዓተ ትምህርቱ መመማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
    • የሥርዓተ ትምህርቱ ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ /ካሌንደር
    • የመምህራን ሥልጠና እና መልእክቶች
    • መጻሕፍቱን ለማግኘት እና ተጨማሪ መረጃ
    • ልዩ ልዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች
  • ፕሮጀክቶች
  • መዝሙረ ማኅሌት
    • የመስከረም ወር መዝሙሮች
      • የዮሐንስ መዝሙር
      • የመስቀል መዝሙሮች
      • የብዙኃን ማርያም መዝሙር (መስከረም ፳፩ )
      • የዘመነ ጽጌ መዝሙር
    • የጥቅምት ወር መዝሙሮች
      • የአብርሃ ወአጽብሐ መዝሙር (ጥቅምት 4 ቀን)
    • የኅዳር ወር መዝሙሮች
      • የቅዱስ ሚካኤል መዝሙር (ኅዳር 12 ቀን)
    • የጥር ወር መዝሙሮች
      • የዘመነ ጥምቀት መዝሙር
      • የቃና ዘገሊላ መዝሙር (ጥር 12 ቀን)
    • የመጋቢት ወር መዝሙሮች
      • የወርኃ ጾም መዝሙሮች
      • የሆሣዕና መዝሙራት
      • የሰሙነ ሕማማት መዝሙሮች
  • ዜና
    • አጫጭር ዜናዎች
    • ዝርዝር ዜናዎች
    • ወቅታዊ መረጃዎች
    • ማስታወቂያ
      • የሰንበት ትምህርት ቤቶች መጻሕፍት እንግሊዝኛ ትርጉም ሥራ ተሳትፎ ጥሪ
  • ያግኙን
  • ቋንቋ
    • ትግርኛ
    • Afaanoromo
  • Menu Menu

መዝሙር - በጌቴ ሴማኔ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/1.-በጌቴ-ሴማኒ.mp3

በጌቴ ሴማኔ በአትክልቱ ቦታ(2)

ለኛ ሲል ጌታችን በዓለም ተንገላታ(2)

አዳምና ሔዋን ባጠፉት ጥፋት(2)

እኛም ነበረብን የዘለዓለም ሞት(2)

ድንግል አልቻለችም ዕንባዋን ልትገታ(2)

እያየች በመስቀል ልጇ ሲንገላታ(2)

መስቀል ተሸክሞ ሲወጣ ተራራ(2)

ይገርፉት ነበረ ሁሉም በየተራ(2)

በአምላክነቱ ሳይፈርድባቸው(2)

እንዲህ ሲል ጸለየ አባት ሆይ ማራቸው(2)

ተጠማሁ፣ተጠማሁ፣ተጠማሁ፣ ሲላቸው(2)

ሆምጣጤ አመጡለት በሰፍነጉ ሞልተው(2)

በረቂቅ ጥበቡ ሁሉን የፈጠረ(2)

በሰዎች ተገርፎ ሞቶ ተቀበረ(2)

(ሢራክ ታደሰ)

መዝሙር - ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/2.-ቅዱስ-ቅዱስ.mp3

ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ አባት ለኛ ተንገላታ

ባምስቱ ቅንዋት እጅ እግሩ ተመታ

አዳምና ሔዋን የመጡትን ዕዳ

በመስቀል ሰባብሮ አዳነን ከፍዳ

የጠላትን ቀንበር በመስቀል ሰባብሮ

ነፃ አወጣን ጌታ ሞትን በሞት ሽሮ

አዝ……

ነውር የሌለበት ንጹሕ ቅዱስ ሲሆን

ደሙን አፈሰሰሰ ለኛ ቤዛ ሊሆን

አዝ…..

ተጠማሁ እያለ እሱ በመስቀል ላይ

እንኩ ጠጡ ብሎ ደሙን ለእኛ ሰጠን ኃጢአት ለማስተሰረይ

አዝ….

መካነ ምሥጢራት አንቺ ጎልጎታ

ወድቆ ተነሣብሳብሽ የዓለሙ ጌታ

አዝ…..

(ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል)

መዝሙር - ቸሩ ሆይ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/3.-ቸሩ-ሆይ.mp3

  ቸሩ ሆይ(2) ለእኛ ብለህ ተሰቀልክ ወይ

ሔዋን ብትበድል እንዲህ እንደዋዛ(2)

መጣ ተሰቀለ የዓለሙ ቤዛ(2)

አዝ…..

የተከሰሰበት ወንጀሉ ቢወራ(2)

ለምጽ ስላነጻዕውር ስላበራ(2)

አዝ……

አንካሳን ማዳኑ ማቅናት ጎባጣውን(2)

ለፍርድ አቀረቡት እውነት የሠራውን(2)

ባህልን ለውጧል ሰንበትንም ሽሯል(2)

ይህ በደለኛ ነው መሞት ይገባዋል(2)

አዝ…..

ብለው ስለአወጁ ባንድነት ሁሉም

ለእኛ ተሰቀለ መድኃኔዓለም

አዝ…

(ሲራክ ታደሰ)

መዝሙር - ሙታንን ያድን ዘንድ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/4.-ሙታንን-ያድን-ዘንድ.mp3

ሙታንን ያድን ዘንድ የሞት ሞትን ሽሮ(2)

ወልደ አምላክ ሄደ ወደ ኋላ ታሥሮ(2)

ምን በበደለ ነው ምን ባደረገ ነው(2)

ወልድ እንደ ቀማኛ ሲገረፍ የዋለው(2)

ቅዱሳን እጆቹ አዳምን የሠሩት(2)

ቅዱሳን እግሮቹ በገነት የዙሩት(2)

ተቸንክረው ዋሉ በጠንካረው ብረት(2)

ግርማን ለኪሩቤል ያጎናጸፋቸው

ዘውድን ለሱራፌል የሚያቀዳጃቸው

ከለሜዳ ለብሶ ዋለ ከፊታቸው(2)

ሔዋን በፈጸመችው የበደልን ሥራ

አዳም በፈጸመች የበደልን ሥራ

ቸሩ ወልደ አምላክ ዋለ በመከራ(2)

ጌታ በፈቃዱ አጁን ቢሰጣቸው(2)

ተዘባበቱበት የሾህ አክሊል ደፍተው(2)

ትንሹም ትልቁም ሲዘባቱብህ(2)

ዋ ምን ይደንቃል ታላቁ ትዕግስትህ

             (ታዕካ ነገሥት በዓታ ሰንበት ት/ቤት)

መዝሙር - የአብርሃም አምላክ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/5.-የአብረሃም-አምላክ.mp3

የአብርሃም አምላክ የይስሐቅም ቤዛ

ወገኖቹን ሁሉ በራሱ ደም ገዛ

የሐሰት ምስክር አቁመው ከሰሱት

በሞት እንዲቀጣ ሁሉም ፈረዱበት

ጲላጦስ ገረፈው በሰንሰለት አስሮ

በአይሁድ መካከል እንዲኖር ተከብሮ

ድንግል አልቻለችም ዕንባዋን ልትገታ

እያየች በመስቀል ልጇ ሲንገላታ

በብርሃን ዙፋን ላይ የቆሙት እግሮቹ

በችካር ላይ ቆሙ ምንም አልሰለቹ

የብርሃን አክሊልን ለሰማዕት ያደለ

የሾህ አክል ደፍቶ ቀራንዮ ዋለ

(መዝሙረ ስብሐት)

መዝሙር - ሞተሃና ስለ እኔ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/6.-ሙተሃልና-ስለኔ.mp3

ሞተሃና ስለኔ ምንም ሳይኖርብህ ጥፋት

በሐሰት ተከሰህ በጲላጦስ ፊት

ኢየሱስ አምላከ ምሕረት ስብሐት ለከ

ያንተ መንገላታት ሁል ጊዜ ያሳዝናል ሲወራ

በመስቀል ላይ ስለ እኛ ያየኸው መከራ

ኢየሱስ የሕይወት እንጀራ ስብሐት ለከ

ከልዑል ቦታ ዝቅ ብለህ ፈጣሬ ፍጡራን አምላክ

በመስቀል ተሰቅለህ ስለሰው የሞትክ

በመስቀል ላይ ተጠማሁ እያልክ ስብሐት ለከ

ክፉ አድራጊዎች ተነሥተው በምቀኝነት መንፈስ

ብዙ ሲጣጣሩ ለደምህ መፍሰስ ስብሐት ለከ

መሐሪ ጌታ አሁንም እንደ ቸርነትህ ብዛት

የኛን በደል ሁሉ ሳትመለከት

አድነን ከዳግም ሞት ስብሐት ለከ

(ሢራክ ታደሰ)

መዝሙር - አምላክ ሆይ ወደኛ ባትመጣ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/9.-አምላክ-ሆይ-ወደእኛ-ባትመጣ.mp3

አምላክ ሆይ ወደኛ ባትመጣ ለብሰህ የማርያምን ሥጋ(2)

ባክኖ የኖረው የአዳ ዘር ውጤቱ ነበር የሚያሰጋ(2)

በዚያች ዓመት በዚያች ወር በዚያች ቀን

ድህነትን ለሰው ልጅ ስትሰጥ(2)

ምን ይበዛ ነበር ትሕትናህ፣ ትዕግሥትህ የማይለወጥ(2)

የሾህ አክል ደፍተህ በራስህ ጎንህን ሲወጉህ በጦር(2)

አንተ ግን ለነረሱ ካባትህ ምሕረትን ስትጸልይ ነበር(2)

ግን መቼ አወቁት እነርሱ በኃጢአት ደንድኖ ልባቸው(2)

መድኃኒታቸውን ገረፉህ ሰቀሉህ አንተም ሞትክላቸው(2)

ዳግም ስትመጣ ለፍርድ ከዓለም ፍጻሜ በኋላ(2)

እንዴት ዕድለኞች ናቸው ካንተ የሚያኙት ተድላ(2)

በዚያች በደብረ ዘይት ቦታ  ደስታን ለቅሶ ሲፈልቅ(2)

ከቶ ወዴት ይሆን ዕድሌ ያንጊዜ የኔ አወዳደቅ(2)

የፀፀጽ ሮሮ በፊትህ እንዳያቃጥለኝ እኔን(2)

እርዳኝ ፈጣሪዬ ካሁኑ አንጻው የዛገው ልቤን(2)

                             (የሺህ እመቤት)

መዝሙር - ወአንቲኒ ቀራንዮ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/10.-ወአንተኒ-ቀራንዮ.mp3

ወአንቲኒ ቀራንዮ መካነ ጎልጎታ(2)

እስመ በኃቤኪ(2) ተሰቅለ መድኃኔዓለም

(ቅዱስ ያሬድ)

መዝሙር - አልፋና ዖሜጋ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/12.-አልፋና-ኦሜጋ.mp3

አልፋና ዖሜጋ ፈጣሪ የሆንክ

በከሐዲዎች እጅ ተይዘህ ቀረብክ

ተገረፍህ ተሰቅለህ በጥፊ ተመታህ

እየደበደቡ ተዘባበቱብህ

ጽድቅን ስለሠራህ በወንጀል ከሰሱህ

ለአዳም ቤዛ ብለህ ብዙ ተንገላታህ

አዝ….

ቅዱሳን እችህ የፍጥኝ አሥረው

ሲገርፉህ ክፉዎች ይቀር አልካቸው

የሁሉ ፈጣሪ ሁሉን የምታውቅ

ዘበቱብህ መቱህ ሸፍነው በጨርቅ

አዝ….

በዚህ አደባባይ ከጲላጦስ ዘንድ

አሳልፈው ሰጡህ ጨካኞች ለፍርድ

ከሐና ቀያፋ ከካህናት ደጅ

ከነሄሮድስ ዘንድ አቀረቡህ በአዋጅ

አዝ….

ግርፋት ሕመሙ አልበቃ ብሎህ

መስቀል ላይ ልትውል ተፈረደብህ

ሣዶር እና አላዶር ዳናትና አዴራ

ተፈልገው መጡ ለችካር በተራ

አምስን ችንካሮች ቅንዋተ መስቀል

አይሁድ አመጡ ሥጋህን ለማቁሰል

አዝ…..

የሰላም ባለቤት አካልህ ተወጋ

ሊወጋ በችንካር እጅህ ተዘረጋ

ግፈኞች አይደሁድ በአንተ ላይ ቀለዱ

ምራቅን ተፉብሕ አንተን ሊጎዱ

አዝ….  (በየነ ድንቁ፣ ዜማ ኪነ ጥበብ)

መዝሙር - ዘጠኝ ሠዓት ሲሆን

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/13.-ዘጠኝ-ሰዓት-ሲሆን.mp3

ዘጠኝ ሠዓት ሲሆን ጌታ ሆይ በመስቀል ሆነህ ጌታ ሆይ

ድምፅን በማሰማት ጌታ ሆይ ነፍስህን ሰጠህ ጌታ ሆይ

አዝ…

የሰማይ ከዋክብት በሙሉ አዘኑ

ጨረቃና ፀሐይ ምስክሮች ሆኑ

ብርሃናት ጨለሙ ጠፍተው ተለያዩ

ሥጋህ በመስቀል ተገልጦ ስላዩ

አዝ……

ጌታችን ክርስቶሽ በመስቀል ላይ ሳለ

አሰምቶ ጮኸ ተጠማሁ እያለ

ማርና ወተትን ለሚመግበው

ሐሞት አመጡለት ቅመሰው ብለው

አዝ…..

ቀኝ ጎኑ ሲወጋ ውሃና ደም ፈሰሰ

በምድር ተረጭቶ ዓለሙን ቀደሰ

የእስራኤል ልጆች ዋይ ዋይ ሲሉልህ

ለእነርሱ አዘንክ እንጂ ለራስህ አላሰብህ

አዝ….

እናትህ ስታለቅስ በመስቀል ሥር ሆና

ዮሐንስን ሰጠሃት ጠብቆ እንዲጽናና

መላእክት ታዩ አጋንንትም ሸሹ

የአይሁድ ሠራዊት ፈርተው ተረበሹ

አዝ….

(በኅብረት)

ዘጠኝ ሠዓት ሲሆን ጌታ ሆይ በመስቀል ሆነህ ጌታ ሆይ

ድምፅን በማሰማት ጌታ ሆይ ነፍስህን ሰጠህ ጌታ ሆይ

(በየነ ድንቁ፣ ዜማ ኪነ ጥበብ)

መዝሙር - ምድረ ቀራንዮ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/16.-ምድረ-ቀራንዮ.mp3

ምድረ ቀራንዮ ምድረ ጎልጎታ

የዓለም መድኃኒት ባንቺ ተንገላታ

መስክሪ አንቺ ምድር ግኡዚቷ ስፍራ

መድኃኒት ክርስቶስ ያየብሽ መከራ

ሁሉን ማድረግ ሲችል ሥልጣን ሲኖረው

የመስቀል ኃፍረት ፍጹም ታገሠው፣

አዝ…..

እጆቹና እግሮቹን በችንካር ለመታው

ይቅርታ አደረገ ለበደለው ሰው

በመስቀል ላይ ሆኖ ተጠማሁኝ እያለ

ለቤዛ ዓለሙ ቀራንዮ ዋለ

አዝ……

ደሙ እንደ ውሀ ሲወርድ በመስቀሉ ላይ

መከራን ሲቀበል ኃያሉ አዶናይ

መከራ በተራ ሲፈራረቅበት

በደል አልተገኘም ከሱ አንደበት

አዝ…..

ከሰማያት ወርዶ እንዲህ መዋረዱ

ለኛ ሲል ነውኮ ሰውን በመውደዱ

ቸሩ መድኃኔዓለም እባክህ ማረኝ

ኃጢአቴንም አይተህ አንተ ይቅር በለኝ

አዝ……

(በየነ ድንቁ)

መዝሙር - ስብሐት ለእግዚአብሔር

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/17.-ስብሐት-ለእግዚአብሔር.mp3

ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት(2)

ወሰላም በመድር ሥምረቱ ለሰብእ ሃሌ ሉያ

ሃሌ ሉያ(3) አሜን ሃሌ ሉያ

(ቅዱስ ያሬድ)

መዝሙር - መድኃኔዓለም

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/18.-መድኃኔዓለም.mp3

መድኃኔዓለም ዘቆምክ በቅደመ ጲላጦስ

መድኃኔዓለም ዘቆምከ በዓውደ ሄሮድስ

ቀራንዮ(2) በዚያ ቦታ

ቀራንዮ(3) ምድረ ጎልጎታ

እጅ እግርህ ታሥረህ በራስህ ፈቃድ

ተገፋህ ተንገላታህ በእደ አይሁድ

ለሸክም ዳረጉህ ለማይቻል ግንድ

አዝ…

እናትህ ስታለቅስ ስለ አንተ መከራ

በቀኖት ሲወጉህ ደምህም ሲዘራ

የራሔልም ልቅሶ በነርሱ ደረሰ

ኀዘን ተሰማቸው ዕንባቸው ፈሰሰ

አዝ….

አይሁድ ባሰባቸው ያዛቸው ጭካኔ

ምራቅን ተፉበት ገረፉት ወይኔ

ዳዊት በገናውን እየደረደረ

አገቱኒ ብሎ ትንቢት ተናገረ

አዝ……(በየነ ድንቁ)

መዝሙር - እስመ ለዓለም ምሕረቱ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/19.-እስመ-ለዓለም-ምሕረቱ.mp3

እስመ ለዓለም ምሕረቱ(4)

አያልቅም ብዙ ነው የአምላክ ቸርነቱ(2)

አመሰገኑት ጌታን ሁላችሁ በአንድነት(2)

መሐሪ ነውና ለሰው ልጆች ሕይወት

አዝ…..

የማይሞተው ሞቶ የተቀበረው(2)

በእሳተ ገሃነም እኛን ሊያድን ነው(2)

አዝ….

ከማርያም የነሣው ያ ቅዱስ ሥጋው(2)

በመስቀል ላይ ሲውል የሚያሳዝነው ነው(2)

አዝ……

በፈጠረው ፍጥረት ለሕማም ተሰጥቶ

ነፍሳትን አወጣ ከሲኦል ጎትቶ(2)

አዝ…መ…(ተምሮ ማስተማር)

መዝሙር - ፍቅር ሰሐቦ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/20.-ፍቅር-ሰሐቦ.mp3

ፍቅር ሰሐቦ ለወልድ ኃያል እመንበሩ(2)

ወአብጽሖ(3) እስከ ለሞት(2)

መዝሙር - አምላክ ለኛ ብሎ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/21.-አምላክ-ለእኛ-ብሎ.mp3

አምላክ ለኛ ብሎ ቢያፈሰው ደሙን

ለምን ከለከለች ፀሐይ ብሃኗን

አንቺ ዕለተ ዓርብ ከሁሉ በለጥሽ

ለማያልቀው ሥጋ ገበያ ሁነሽ

ከማያለውቀው ሥጋ ሰዎቹ ቢበሉ

ገነት ገብተው ቀሩ ሳይከለከሉ

የከበረው ሥጋ የከበረው ደም

በመስቀል ላይ ዋለ ኢየሩሳሌም

በሥጋችን ሐኪም ዓለም ተታለለ

ነፍስን የሚያድናት ደጉ ሐኪም ሳለ

ይኸው ደጉ ሐኪም የማይፈልግ ዋጋ

ነፍሥንም ሥጋን ያድናል ካደጋ

መዳን የምትፈልግ ላሳይህ ቤቱን

በሰላም ጠይቃት ቤተ ክርስቲያንን

(ዶ/ር ኢሳይያስ ዓለሜ)

መዝሙር - የሾህ አክሊል

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/22.-የሾህ-አክሊል.mp3

የሾህ አክሊል ጉንጉን ደፍተው በራሱ ላይ

ብለው ዘበቱበት የአይሁድ ንጉሥ ሆይ

በጉልበታቸውም ተንበርከኩና

ሰላም ለአንተ ይሁን አሉት አፌዙና

ራሳቸውንም እየነቀነቁ

መንገደኞች ሁሉ በጌታ ላይ ሳቁ

አወይ ሌለውን ሰው ያድን የነበረው

ምነዋ ራሱን ሳያድን የቀረው

እያሉ ሲነቅፉት በእርሱ ያላመኑ(2)

ምልክት ከሰማይ ታየ ወዲያዉኑ(2)

ፀሐይም ጨለመ ደም ሆነች ጨረቃ(2)

ከዋክብት ረገፉ ዓለት ሁሉ ነቃ(2)

የመቅደሱ ግርዶሽ ከሁለት ሲቀደድ(2)

የሞቱት ተነሡ ከመቃብር ጉድጓድ(2)

መዝሙር - አለኝታችን

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/23.-አለኝታችን.mp3

አለኝታችን(2) ይሁን ፈጣሪያች(2)

እሱ ስለሆነ(4) የሕይወት ተስፋች(2)

ኢየሱስ ክርስቶስ ተሰቅሎ(2) በቅዱስ መስቀሉ(2)

ፍጹም ሰላም ሆነ (4) ለአዳም ልጅ ሁሉ(2)

ለምታለፍው ዓለም (2) በጨነቅ ይቅርብን(2)

ተስፋችንም ሁሉ (4) በክርስቶስ ይሁን(2)

(ብርሃኑ ውድነህ)

መዝሙር - ፀሐይ ሐዋርያ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/24.-ፀሐይ-ሐዋርያ.mp3

ፈያታዊ ዘየማን መኑ መሀረከ

ወመኑ ነገረከ ታእምር ዘንተ

ነቢያተ ኢሐተትኩ ወሐዋርያተ ኢተሎኩ

አላ ፀሐይ ቀፀበተኒ ሶበ ርኢኩ አመንኩ

ኃይለ መስቀሉ መድኃኒተ ኮነኒ

* * *

መድኃኒቴ አንተነህ ጠባቂ እረኛዬ(2)

በመስቀልህ ምራኝ አቤቱ ጌታዬ(2)

በመስቀል ከአንተ ጋር አብሮ የነበረው(2)

ገነትን ወረሰ እሱ እንደተመኘው(2)

ነቢያትም ሆኑ ደግሞም ሐዋርያት(2)

ያተን መስቀል ቀድመው ሳይሰብኩት(2)

በመንግሥትህ ጌታ አስበኝ እያለ(2)

ወዳንተ ጸለየ በመስቀል ላይ ሳለ(2)

ወዳንተ ለመነ ምንም ሳይሰለች(2)

የእርሱም ሐዋርያ ፀሐይ ነበረች(2)

ፀሐይም ያን ጊዜ ፈጥና ጠቀሰችው(2)

የገነት ማኅተም ወዲያው ተሰጠችው(2)

(ቅዱስ ያሬድ፣ መዝሙረ ስብሐት)

መዝሙር - ተፈጸመ አለ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/25.-ተፈጸመ-አለ.mp3

ተፈጸመ አለ ጌታ ነፍሱን ሰጠ

ስለኔ ኃጢአት በመከራ አለፈ

ደፋ ቀና እያለ ሲወርድ ሲንገለታ

ያ ብርሃን ፊቱ በጥፊ ተመታ

አዝ……

በሐሰት ተከሶ በሐሰት ተገደለ

በውርደት ሸንጎ ፊት ባደባባይ ዋለ

በውሀ ጥም ዛለ በረሀብ ተቀጣ

ስለ ሰው ልጆች ሲል የሞት ጽዋን ጠጣ

አዝ….

አንቺ ዕለተ ዓርብ እንዴት ያለሽው ነሽ

ሰማያዊ አባት የተሰቀለብሽ

ከኋላ ከፊቱ በጠላት ተከሶ

ማንም አልነበረም የሚያናናው ከቶ

አዝ…..

ርኁሩኅ ጌታዬ ስኔ ብለህ ነው(2)

ያንን ሁሉ መከራ በትዕግሥት ያለፍከው

አዝ…..         (ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል)

Search Search

Recent Posts

  • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ
  • ሦስተኛ ዙር የ፲፪ ክፍል ምርቃት መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት ተከናወነ።

Archives

  • April 2026
  • September 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • May 2025
  • April 2025
  • October 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • July 2022
  • June 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
© Ethiopian Orthodox Church Global Sunday School Union | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
  • Link to Youtube
  • Link to Telegram
  • Link to TikTok
Link to: የሆሣዕና መዝሙራት Link to: የሆሣዕና መዝሙራት የሆሣዕና መዝሙራት Link to: የብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት Link to: የብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት የብፁዕ አቡነ ቀሌምንጦስ የእንኳን አደረሳችሁ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top