ርእይ
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሚቋቋሙ ሰንበት ት/ቤቶች የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እምነት ሥርዓትና ትውፊት የሚያውቅ፣ አስተዳደራዊና መንፈሳዊ አገልግሎቷን የሚረከብ፣ በሥነ ምግባር የታነጸ እና በሀገራዊም ሆነ በዓለም ዓቀፋዊ የለውጥ ክሥተቶች ላይ በጎ ተጽዕኖ መፍጠር የሚችል ብቁ ትውልድ ሲያፈሩ ማየት
ተልእኮ
በየደረጃው የሚቋቋሙ የሰንበት ት/ቤቶችን አንድነት በማጠናከር እና ማዕከላዊ አሠራር በማስፈን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት፣ ሥርዓት እና ትውፊት የሚያስተምሩ እና የሚያስጠብቁ ሰንበት ት/ቤቶችን በማደራጀት፣ በማጠናከርና፣ በማስተባበር የቅድስት ቤተክርስቲያንን ሐዋርያዊ አገልግሎት በሀገር አቀፍ ደረጃ ብሎም በመላው ዓለም እንዲያስፋፉ ማስቻል፡፡
ዕሴቶች
መንፈሳዊነት፣ አንድነት፣
መደጋገፍ ፣ ቀጣይነት፣ አገልጋይነት
ክርስቲያናዊ ኃላፊነት፣ ጽናትና ምስክርነት
በፍቅር የኾነ አገልግሎት
ዘመኑን መቅደም