ርእይ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የሚቋቋሙ ሰንበት ት/ቤቶች የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እምነት ሥርዓትና ትውፊት የሚያውቅ፣ አስተዳደራዊና መንፈሳዊ  አገልግሎቷን የሚረከብ፣ በሥነ ምግባር የታነጸ እና በሀገራዊም ሆነ በዓለም ዓቀፋዊ የለውጥ ክሥተቶች ላይ በጎ ተጽዕኖ መፍጠር የሚችል ብቁ  ትውልድ ሲያፈሩ ማየት

ተልእኮ

በየደረጃው የሚቋቋሙ የሰንበት ት/ቤቶችን አንድነት በማጠናከር  እና ማዕከላዊ አሠራር በማስፈን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት፣ ሥርዓት እና ትውፊት የሚያስተምሩ እና የሚያስጠብቁ ሰንበት ት/ቤቶችን በማደራጀት፣ በማጠናከርና፣ በማስተባበር የቅድስት ቤተክርስቲያንን ሐዋርያዊ አገልግሎት በሀገር አቀፍ ደረጃ ብሎም በመላው ዓለም እንዲያስፋፉ ማስቻል፡፡

ዕሴቶች

መንፈሳዊነት፣ አንድነት፣

መደጋገፍ ፣ ቀጣይነት፣ አገልጋይነት

ክርስቲያናዊ ኃላፊነት፣ ጽናትና ምስክርነት

በፍቅር የኾነ አገልግሎት

ዘመኑን መቅደም

ወቅታዊ ጉዳዮች

“ልባችሁ በጸጋ ቢጸና መልካም ነው እንጂ በመብል አይደለም” ዕብ. ፲፫፡፱

“ልባችሁ በጸጋ ቢጸና መልካም ነው እንጂ በመብል አይደለም” ዕብ. ፲፫፡፱

የኢትዮጵያ አብዛኛው ሕዝብ ባለሥልጣናቱ እንደሚያወሩት የተመጣጣነ ምግብ የሚያውቅ፣ በቀን ሦስት ጊዜ የሚመገብ አይደለም። ነገር ግን...
በመንፈስ ቅዱስ የተቃኙ አባቶች

በመንፈስ ቅዱስ የተቃኙ አባቶች

ንግሥቲቱ ገንዘቧን ሁሉ ለባለመድኃኒት ሰጥታ ብትጨርስም...
የነገረ ሰብእ ትምህርት ጉድለት የወለደው አገራዊ ቀውስ

ከወርቃማው ሕግ አትንሸራተቱ (የነገረ ሰብእ ትምህርት ጉድለት የወለደው አገራዊ ቀውስ ክፍል ሁለት)

በተግባር ባይመራበትም ዐለሙም ወርቃማ ሕግ በማለት የሚጠራው...
ብሔር ተኮር ሃይማኖታዊ ስብከት

ብሔር ተኮር ሃይማኖታዊ ስብከት

በኦሮምያ ክልል የሚገኙ ጥቂት የቤተ ክርስቲያኗ አገልጋዮች ፖለቲካውን ተገን አድርገው አሐቲነቷን በሚፈታተን መንገድ...

የአንድነቱ መልእክት

ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት

ዘመንን በአግባቡ መሻገር የሚቻለው የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ወቅቱን ጠብቆ እንደየዘመኑ አኗኗር አቀራረቡን እና ተደራሸነቱን በማስፋት ሲሆን ጉዞው ዕድልና ችግርን ጎን ለጎን የሚያስተናገዱበት በመሆኑ በቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ መሠረት ቅዱስ ጳውሎስ ለክርስቲያኖች ባስተማረው ትምህርት “ የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሯችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ፣የኑሯቸውን ፍሬ እየተመለከታችሁ በእምነታችሁ ምሰሏቸው፡፡ ዕብ 13፡7 ያለውን መሠረት በመጠበቅ እና አሁን ያለውን የአገልግሎት ከባቢ በመረዳት ለሰ/ት/ቤቶች አገልግሎት ውጤታማነት አሁን የምናየውን ፈተና ለማለፍ በስትራቴጂ ማገልገል እና ልዩ ልዩ ችግሮችን እንደ አመጣጣቸው ለማለፍ በትጋት የመሠራት ስልትን መዘርጋት ላይ ይተጋል፡፡ “ ቀኖች ክፉዎች ናቸው እና ዘመኑን ዋጁ” ኤፌ5፡16

በፌስቡክ ያግኙን

መልእክታት

የቅዱስ ፓትርያርኩ መልእክት

የሰ/ት/ቤቶች አንድነት መጠንከር አለበት ። የሰ/ት/ቤቶች መዋቅር ዓለም አቀፋዊ አገልግሎት እና ቤተ ክርስቲያን ኃላፊነት የሰጠችው መዋቅር ነው፡፡ ለዚህም በሀሉም መዋቅር በአንድነት ሥትሠሩ ለቤተ ክርስቲያን ፀጋ ለእኛም ደስታችን ናችሁ፡፡

በ2013 ዓ.ም ዓመታዊ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ መልእክት የተወሰደ

የመምሪያው ሊቀ ጳጳስ መልእክት

የቤተ ክርስቲያናችን ተተኪ ትውልድ የሚፈራበት ተቋም ነው። ከትውልድ ወደ ትውልድ የቤተ ክርስቲያንን አስተምህሮ በመጠበቅ እና በማስጠበቅ ለማስቀጠል በዚህ ዘመን ሰ/ት/ቤቶች አንድነት በጣም አስፈላጊ እና ተመሳሳይ አገልግሎት በሁሉም ቦታ ሥርዓቱን ጠብቆ ለማድረስ የሚረዳ በቅዱስ ሲኖዶስ ሕግ ተሰጥቶት በሁሉም የቤተ ክህነት መዋቅር የሚሠራበት ግዙፍ መዋቅር ነው፡፡ ለዚህም ሁሉም የቤተ ክርስቲያን አካል በሙሉ ቅድሚያ ሰጥቶ ድጋፍ እና እንክብካቤ ሊያደርግ ይገባል፡፡

በ2013 ዓ.ም ዓመታዊ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ መልእክት የተወሰደ

አስተያየትዎን ይጻፉልን