እንደሚታረዱ በጎች ሆንን!

እንደሚታረዱ በጎች ሆንን!

እንደሚታረዱ በጎች ሆንን!

እንደሚታረዱ በጎች ሆንን!

ኢትዮጵያ አገራችን ለረጅም ዘመናት በአኩሪ ባህልና እሴት አሸብርቃ ከእኛ ደረሰች ናት። ለዚህ መልካም እሴት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሚና ጉልህ ነው። ከቅርብ ዓመታት ወዲህ ግን ወርቅ ላበደረ ጠጠር እንዲሉ ቤተ ክርስቲያን የጥቃት ዒላማ ሆና ብዙ ቀስቶች ሲወረወሩባት ታያል። መንግሥትም አጥፊዎች ላይ ርምጃ ከመውሰድ ይልቅ የጥፋቱ አካልና ተባባሪ በሚመስል መልኩ በገቢርና በዝምታ አጋዥነቱን አሳይቷል። በተለይም የኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግሥት በኦርቶዶክሳውን ላይ እየተፈጸመ ያለውን ጥቃት እንዲያስቆም ሲጠየቅ ጥቃቱን ከመካድ ጀምሮ በግልጽ አጥፊዎችን እስከ መደገፍ የደረሱ ድጋፎችን ሲያደርግ ተስተውሏል፡፡ ቁጣውና ጩኸቱ ጠንከር ሲል ጥቃቱን ለማስቆም ቃል ይገባል፤ ነገር ግን ጩኸቱ በረድ ሲል የተናገረውን ሲፈጽም አይታይም፡፡ እንዲህ መሆኑ ለገዳዮች የልብ ልብ ሰጣቸው፡፡ ቤተ ክህነቱም የክርስቲያኖች ግድያና ስቃይ ደንታ የሚሰጠው አይመስልም። በየቦታው ክርስቲያኖች ሲገደሉ ምንም ካለማለት ደረጃ የደረሰው ምን ነክቶት ነው ያሰኛል፡፡ በአርሲ ዞን የተፈጸመውን ጅምላ ጭፍጨፋ በተመለከተ ኅዳር ፳፬ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም ያወጣው መግለጫም “የእንጦጦ መምህር ቢናገር በዓመት፣ ያውም እሬትን” የሚያስተርት ነው። የተሰጠው መግለጫ በሟቾቹ ከመቀለድ አይተናነስም፡፡ ችግሩን ለመንግሥትም ሆነ ለዓለም ማኅበረሰብ ለመግለጥ ካስፈለገ በሚገባ አደራጅቶ፣ ብስሉን ከጥሬ ለይቶ፣ እውነት የሆነውን ሐሰት ከሆነው አጣርቶ ነው፡፡ ይህ መግለጫ ግን ድብስብስ ያለ፣ ዓላማው የማይታወቅ ነው፡፡ ቢሆንም ግን በክርስቲያኖች ላይ እየደረሰ ያለው መከራ ማቆሚያ የሌለው፣ ለማስቆም ፍላጎት ያለው የመንግሥት አካልም የሌለ መሆኑን የሚያስገነዝብ መሆኑን መረዳት ይገባል።
በመላ ሀገሪቱ ክርስቲያኖች ተመርጠው መገደል የጀመሩት ኢሕአዴግ ደርግን አስወግዶ ሥልጣን ከያዘ ማግስት ጀምሮ መሆኑ እንደተጠበቀ ሆኖ ለውጥ መጣ ከተባለበት ጊዜ ጀምሮ ግን ተጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ በተለይም ከሐምሌ ፳፰ ቀን ፳፻፲ ዓ.ም በጅግጅጋ የተጀመረው ክርስቲያኖችን መርጦ ማጥቃት በመቀጠልም በኦሮሚያ ክልል ምክንያት እየተፈለገ፣ ወፍ በበረረ፣ ዘንግ በተወረወረ ቁጥር ለመከራ ተዳርገዋል፡፡ የዓይናችሁ ቀለም አላማረንም፣ ሃይማኖታችሁን አልወደድነውም እየተባሉ በስቃይ ላይ ቢገኙም ችግሩን የሚፈታላቸው፣ ጩኸታቸውን የሚሰማቸው አልተገኘም፡፡ ይህ ብቻ ሳይሆን በአማራ ክልል ከሚሴ ዞን፣ በ፳፻፲፩ ዓ.ም ሲዳማን ራሷን የቻለች ክልል ለማድረግ መንግሥትን ጠይቀው መልስ የተነፈጋቸው የዞኑ ነውጠኞች ጥያቄውን ውድቅ ያደረጉባቸው ኦርቶዶክሳውያን የሆኑ ይመስል ከየቤታቸው እየተፈለጉ ለሞትና ለመከራ ዳረጓቸው፡፡ ሀብት ንብረታቸው ወደመ፣ ይዞታቸው እየተነጠቀ ለሌላ አካል ተሰጠ፡፡ አብያተ ክርስቲያናት ተቃጠሉ፡፡
ጥቅምት ፳፻፲፪ ዓ.ም ጅዋር መሐመድ ከመንግሥት ጋር በነበረው አለመግባባት ተከበብኩ ባለ ጊዜ ለመከራ የተዳረጉት ክርስቲያኖች ናቸው፡፡ ሰኔ ፳፻፲፪ ዓ.ም የአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳን መገደል ተከትሎ በክልሉ በሚኖሩ ክርስቲያኖች ላይ መውረድ የጀመረው የመከራ ዝናብ ዛሬ ድረስ አላቋረጠም፡፡ ክርስቲያኖች በክልሉ እንዳይኖሩ በሕግ ባይከለከሉም በአመፅ እና በጉልበት ከተከለከሉ ግን ዓመታት ማለፋቸው የአደባባይ ምሥጢር ከመሆን ደረጃ ላይ ደርሷል፡፡ በተደጋጋሚ ከመንግሥት ጋር ውይይት ተደርጎ ችግሩን እንፈታዋለን እየተባለ ቃል ቢገባም ችግሩ እየባሰበት እንጂ እየተሻለ አለመምጣቱ ቤተ ክርስቲያን የሐዘን መግለጫ ከማውጣት ያለፈ ተግባር መፈጸም እንዳለባት የሚያስገነዝብ ነው፡፡ ግን ይህ ሲሆን አይታይም።
በሰሞኑ በአርሲ ዞን የተፈጸመውን ጥቃት በተመለከተ ጠቅላይ ቤተ ክህነቱ ባወጣው መግለጫ “በሶሌ ዲገሉ እና ጢጆ ለቡ በተባሉ ቀበሌዎች ፳፰ ኦርቶዶክሳዊያን ከየቤታቸው ተለቅመው የተገደሉ ሲሆን ከእነዚህ ውስጥም ፯ቱ ሴቶችና ፳፩ ወንዶች መሆናቸው ታውቋል። በዚህ ጥቃትም እድሜያቸው ከሰባ ዓመት አዛውንት እስከ ሃያ ስምንት ቀን ጨቅላ ሕጻናት ይገኙበታል። በተመሳሳይ በዲገሉ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ፭ ኦርቶዶክሳዊያን ከመገደላቸው በተጨማሪ የሦስት ኦርቶዶክሳውያን ቤት ደግሞ ሙሉ በሙሉ ተቃጥሏል። ከዚህ ቀደም በሮቤ አንዲቶ ደብረ ምጥማቅ ማርያም ቤተ ክርስቲያን በዓለ ማርያምን አክብረው ወደ ቤታቸው በመመለስ ላይ የነበሩ ሦስት ኦርቶዶክሳዊያን ጨለማን ተገን ባደረጉ ነፍሰ ገዳዮች መገደላቸው ይታወሳል። የሀገረ ስብከቱ የሥራ ኃላፊዎች ከመንግሥት የጸጥታ አካላት ጋር በተደጋጋሚና ሆን ተብሎ በሚፈጸመው የኦርቶዶክሳዊያን ጥቃት ዙሪያ በጋራ እየሠሩ የሚገኙ ሲሆን በዚህ ዐይነት የጥቃት ተግባር ላይ ተሰማርተው የሚገኙ አንዳንድ አካላት ላይ በመንግሥት በኩል የማያዳግም ርምጃ እንደተወሰደባቸው ሀገረ ስብከቱ በላከው ሪፖርት አረጋግጠዋል” በማለት ዘርዝሮታል።
ቢቢሲ አማርኛ የደረሰውን ጥቃት የዘገበው “በጥቃቱ የቤተሰብ አባላት የተገደሉባቸው በሽርካ ወረዳ፣ የጥዮ ለቡ ቀበሌ ነዋሪ፣ ኅዳር ፲፫ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም. ግድያው ሲፈጸም በአጋጣሚ በስፍራው ባለመኖራቸው እርሳቸው ቢተርፉም፣ አብዛኞቹ የቤተሰቦቻቸው አባላት እንደተገደሉባቸው ተናግረዋል። በጥቃቱ ባለቤቴ እና ልጄ፣ የአባቴ ልጆች፣ የአባቴ ሚስት፣ እኅቶቼ እና ወንድሞቼ በአጠቃላይ ሰባት ቤተሰብ ተገድለውብኛል። ከቤት ወስደው ነው የጨፈጨፏቸው” ብለዋል በመሪር ሐዘን። ቢቢሲ ባነጋገራቸው ወቅትም ከጥቃቱ የተረፉ የሁለት ዓመት እና የስምንት ዓመት ልጆቻቸውን አሳክመው እየተመለሱ እንደ ሆነ ተስፋ በቆረጠ ሁኔታ ገልጸዋል። በወረዳው ሾሌ ዲገሊቡና ቀበሌ ነዋሪ የሆኑ ሌላ ግለሰብም ባለፈው ሳምንት በተፈጸመው ጥቃት የስምንት ልጆቻው እናት የሆነችው ባለቤታቸው እና የ፲፪ ዓመት ሴት ልጃቸው እንደተገደሉባቸው ለቢቢሲ ተናግረዋል” በማለት ነው።
ከሳምንት በፊት በደራ ወረዳ በክርስቲያኖች ላይ የተፈጸመው ግድያ በልዩ ልዩ ብዙኀን መገናኛ ተዘግቦ አይተናል ሰምተናልም፡፡ እነዚህ ክርስቲያኖች በሰማዕትነት እንዲጠሩ የአምላካችን ፈቃድ ቢሆንም ከክርስቲያኖች የሚጠበቅ ተግባርና ሐላፊነት መኖሩን መዘንጋት አይገባም፡፡ እንዲህ ያለው አሰቃቂ ግድያ ሲፈጸም ጥቃቱን እንዲያስቆም መንግሥትን ከመጠየቅ ጀምሮ ሌሎች ተግባራትን ማከናወንም ይገባል፡፡ ዝም አላችሁ ላለመባል ብቻ ለግብር ይውጣ የሚሰጡ መግለጫዎች ግን ክርስቲያኖችን ተስፋ ያስቆርጣሉ፡፡ ከዚህ በተጨማሪም በአባቶች ላይ ያለው አመኔታ እንዲቀንስ ስለሚያደርግ ሊታሰብበት ይገባል፡፡ መንግሥትም ዜጎቹን ነቅቶና ተግቶ የመጠበቅ ሐላፊነቱን መወጣት ይኖርበታል፡፡

ይህ ዐይነቱ ኦርቶዶክሳውያን ላይ ያነጣጠረ ግድያ እንዲቆምና የወንጀሉ ፈጻሚዎችም ለፍርድ እንዲቀርቡ በሀገረ ስብከቱ በኩል እየተደረገ ያለው ጥረት እንደተጠበቀ ሆኖ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ጽሕፈት ቤትም በድርጊቱ እጅጉን ማዘኑን እየገለጸ ጉዳዩን ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር በመሆን የሚከታተለው መሆኑን ለመግለጽ እንወዳለን። በሌሎች ስፍራዎች የሚያጋጥሙ ተመሳሳይ ጥቃቶችን በእንጭጩ ለመቅጨትና ከሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ጋር በመነጋገር መፍትሔ ማበጀት ይቻል ዘንድ አህጉረ ስብከት ችግሮች በሚያጋጥሙ ወቅት ሪፖርት እንዲልኩ ቀደም ሲል በደብዳቤ በተላከላቸው የስልክና ዘመናዊ የመገናኛ ዘዴዎች አማካኝነት በፍጥነት በማሳወቅ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ እያሳሰብንና ለሞቱት ኦርቶዶክሳውያን ወገኖቻችን ሁሉ ልዑል እግዚአብሔር መንግሥተ ሰማያትን እንዲያወርስልን በመጸለይ የፌዴራልም ሆነ የክልል መንግሥታት የሚደርሱ ሃይማኖት ተኮር ጥቃቶች እንዲቆሙና መሰል ጥቃት እንዳይፈጸም ለኦርቶዶክሳዊያን ወገኖቻችን ከለላ እንዲሰጡልን እንጠይቃለን̋ ተብሎ የተነገረውን አጠናክሮ መቀጠል እንጂ በቃል እየተናገሩ ከተግባሩ መራቅ ብዙ ዋጋ ያስከፍላል።

ባይተዋርነት እስከ መቼ? ክፍል ሁለት

ባይተዋርነት እስከ መቼ? ክፍል ሁለት

ባይተዋርነት እስከ መቼ? ክፍል ሁለት

ባይተዋርነት እስከ መቼ? ክፍል ሁለት

በክፍል አንድ ጽሑፋችን ኦርቶዶክሳውያን በሀገራችን ባይተዋር ያደረጉንን ጥቂት ምክንያቶች ለማየት ሞክረናል፡፡ በዛሬው ጽሑፋችን ደግሞ ከዚህ ባይተዋርነት የመውጫ መንገዶችን ለመጠቆም እንሞክራን፡፡
1. ለሰማያዊ ክብር፣ ለዘላለማዊ ሕይወት የሚያበቃ መንፈሳዊ ዝግጅት ይኑረን፡- እንደ ቃሉ የምንኖር እምነተ ብርቱዎች እና ከምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን በአግባቡ የምንካፈል መሆን አለብን፡፡ ይህ መንፈሳዊ ዝግጅት እንደ ጥንቶቹ ጽኑ ክርስቲያኖች በአሕዛብ ፊት ያለ ፍርሃት “እኛ የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን” የምንል የዐደባባይ ምስክሮቹ እንድንሆን ያበረታናል፡፡ “ልንሔድ ከክርስቶስ ጋር ልንኖር እንናፍቃለን” ለማለት ያበቃናል፡፡ በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚፈጸመውን በደል ለመቃወም እና ፍትሕ ርትዕ ለመጠየቅ ብሎም ለማስፈን እንድንችል፣ የፍርሃትን መንፈስ ገድለን የኃይልና የሥልጣንን መንፈስ እንድንለብስ ያደርገናል፡፡ Read more

በረሃብ ከመሞት በጦርነት መሞት ይሻላል

በረሃብ ከመሞት በጦርነት መሞት ይሻላል

በረሃብ ከመሞት በጦርነት መሞት ይሻላል

በረሃብ ከመሞት በጦርነት መሞት ይሻላል

ዓለም ለዘመናት የተለያዩ መከራዎችንና ፈተናዎችን አስተናግዳለች። የብዙዎቹ ችግሮች ምንጮች ደግሞ ሰው ሠራሽ ናቸው። ሰው በእግዚአብሔር አርአያ መፈጠሩ፣ ዐዋቂና አስተዋይ ፍጡር መሆኑ ለችግሮቹ መፍቻ ቁልፍ ለማግኘት እንዲችል አድርጎታል። በዚያው ልክ ራሱ ለፈጠራቸው ችግሮች መፍትሔ አጥቶ ሲባዝን ይታያል። በዚህም ምክንያት ሰው የስኬቱ ተጎጂ (the victim of his own success) ሆኗል። Read more

የሰላም ዋጋው ስንት ነው?

የሰላም ዋጋው ስንት ነው?

የሰላም ዋጋው ስንት ነው?

የሰላም ዋጋው ስንት ነው?

ሰላም የሚለው ቃል ሲጠራ ቀላል ቢመስልም ዋጋው ግን በገንዘብ ከመተመን በላይ ነው፡፡ ሰላም እንኳን ለሰው ልጅ ለእንስሳት፣ ለአራዊት እና በጠቅላላው ለሥነ ፍጥረት በጣም አስፈላጊ ነገር ነው፡፡ ሰላም ከሌለ ማንም ወጥቶ መግባት፣ ነግዶ ማትረፍ፣ አርሶ መብላት፣ ደግሶ መዳር አይችልም፡፡ ሠርቶ የመለወጥን ተስፋም ያመነምናል፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በጸሎተ ቅዳሴዋ “እግዚአብሔር በይቅርታው አንድ ያደርገን ዘንድ ስለ ሰላም እንማልዳለን፤ በዘመኑ ሁሉ ፍጹም ሰላምን እግዚአብሔር ይሰጣት ዘንድ እግዚአብሔርን ስለምትወድ ስለ አገራችን ኢትዮጵያ እንማልዳለን” በማለት ዕለት ዕለት ፈጣሪዋን የምታሳስበው ያለ ምክንያት አይደለም – ሰላም የሁሉ ነገር መሠረት ስለሆነ እንጂ፡፡ እንኳን ሰማያዊ ለሆነው ሃይማኖት ለምድራዊ ኑሮም ቢሆን ዓለም የምትሸልመው ሳይታክቱ ለሰላም የደከሙትን ነው፡፡ Read more

ባይተዋርነት እስከ መቼ?

ባይተዋርነት እስከ መቼ?

ባይተዋርነት እስከ መቼ?

ባይተዋርነት እስከ መቼ?

 መስከረም ፲፭ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም. በአርሲ ሀገረ ስብከት በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ ቤተ ክህነት ኦርቶዶክሳውያን ተገደሉ (ሰባት ኦርቶዶክሳውያን)፡፡ ኦርቶዶክሳውያን ጨቅላ ሕፃናትን ጨምሮ የካህናት ቤተሰብ በአሰቃቂ ሁኔታ በጥይት ተደብድበው ተገደሉ፡፡ በርካቶች ቆሰሉ፡፡
 ካህናት እና ቤተሰቦቻቸው ከቤተ ክርስቲያን እስከ ቤታቸው ታድነው ይገደላሉ፡፡
 መስከረም ፳፫ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም.) በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በአዳማ ዙሪያ ወረዳ ቤተ ክህነት በአርቱ መካነ ቅዱሳን ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች የሆኑት አባ ተክለ አብ እና ቀሲስ መሠረት ተገደሉ፡፡ በደራ፣ በወለጋ፣ በቤንሻንጉል ወዘተ
 አሮጌው ዓመት(፳፻፲፭ ዓ.ም.) በስልጤ ዞን የተለመደውን የኦርቶዶክሳውያን ደም በማፍሰስ፣ ሀብት ንብረታቸውን በማቃጠል እና በማሳደድ ነው የተሰናበተን፡፡ አዲሱ ዓመት ደግሞ የአሮጌውን ዓመት የደም ግብር መገበርን አጠናክሮ ቀጥሎበታል፡፡
 ካህኑ በዐውደ ምሕረት በአገልግሎት ላይ እያሉ በጥይት የተመቱት ጠረፍ አካባቢ በምትገኘው አጥቢያ አይደለም፡፡ እዚሁ አዲስ አበባ ነው፡፡ Read more

ክርስትና ከዘውግ ባሻገር የሆነ ማንነት

ክርስትና ከዘውግ ባሻገር የሆነ ማንነት

ክርስትና ከዘውግ ባሻገር የሆነ ማንነት

ክርስትና ከዘውግ ባሻገር የሆነ ማንነት

የሰው ልጅ ሁሉ ከአዳም የተገኘ የእግዚአብሔር አምላክ የእጅ ሥራ ነውና ከላይ በቀለም በቅርፅ ወዘተ ልዩነት ቢኖረው እንኳ የሚመሳሰልበት ከውስጥ የሆነ ሥነ-ሕይወታዊ አንድነት አለው፡፡ ይህም ተመሳሳይ ተፈጥሮአዊ እና ሥነ ልቡናዊ (Bio-Psychic Union) ውቁር እንዲኖረው አድርጓል፡፡ በማኅበራዊ ፍጡርነቱ በፈጠረው በማኅበራዊ መስተጋብሩ ምክንያት ደግሞ በሒደት ራሱን ካንድ የባህል መሠረት ካለው ማንነት ጋር ያዛምዳል፡፡ ይህ ልዩነት ደግሞ የተለያየ አስተሳሰብ/ እና የአረዳድ አድማስ እንዲኖረው ያደርገዋል፡፡ ክርስትና ለነፍሳችን መድኅን የሆነው የእውነትና የሕይወት መንገድ ጌታችን መድኃኒታችን ክርስቶስ ኢየሱስ ብቻ መሆኑን ያስተምራል፡፡ ክርስቲያንም ይህን እውነት ብቻ ይከተላል፡፡ ከአምልኮ መልስ ባለው ማኅበራዊ መስተጋብር ግን ብዝኃነትን ያከብራል፡፡ Read more

ነፋስን ዘርተዋል፤ ዐውሎ ነፋስንም ያጭዳሉ (ሆሴ. ፰፡፯)

ነፋስን ዘርተዋል፤ ዐውሎ ነፋስንም ያጭዳሉ (ሆሴ. ፰፡፯)

ነፋስን ዘርተዋል፤ ዐውሎ ነፋስንም ያጭዳሉ (ሆሴ. ፰፡፯)

ነፋስን ዘርተዋል፤ ዐውሎ ነፋስንም ያጭዳሉ (ሆሴ. ፰፡፯)

ቸርነት የባሕርይ ገንዘቡ የሆነው አምላካችን እግዚአብሔር “ብትወዱኝስ ትእዛዜን ጠብቁ” ብሏል። ትእዛዛቱን በመጠበቅ የሚገኘው ክብር ደግሞ የዘለዓለም ሕይወት መሆኑን ገልጾልናል። የምንጠብቃቸውን ትእዛዛት በተመለከተ ደግሞ አንድ ሕግ ዐዋቂ “ከሕግ ማናቸይቱ ትእዛዝ ትልቅ ናት?” ብሎ በጠየቀው ጊዜ ጌታ የሰጠው መልስ “አምላክህን በፍጹም ልብህ፣ በፍጹም ነፍስህ፣ በፍጹም አሳብህ ውደድ። ታላቂቱ እና ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት። ሁለተኛይቱም ይህችን ትመስላለች። እርስዋም ባልንጀራህን እንደ ነፍስህ ውደድ የምትለው ናት። በእነዚህ በሁለቱ ትእዛዛት ሕግም ሁሉ ነቢያትም ተሰቅለዋል” (ማቱ. ፳፪፡፴-፮፵) የሚል ነው። ከእነዚህ ከሁለቱ ትእዛዛት የሚወጣ ሕግ እና ትእዛዝ የለም። ሁሉም ሕግጋት ፍቅረ እግዚአብሔርን እና ፍቅረ ቢጽን መሠረት ያደረጉ ናቸው። እነዚህን ትእዛዛት ማክበር በምድር ላይ ሰላምን ይሰጣል፤ ዕድሜን ያረዝማል፤ በሰማይ የዘለዓለም ሕይወትን ያስገኛል። Read more

ጸሎታቸው የሚጠቅም ውግዘታቸው የሚጎዳ

ጸሎታቸው የሚጠቅም ውግዘታቸው የሚጎዳ

ጸሎታቸው የሚጠቅም ውግዘታቸው የሚጎዳ

ጸሎታቸው የሚጠቅም ውግዘታቸው የሚጎዳ

ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ ከመንፈሳዊ ብቃት ደረጃ ላይ የደረሰ አባት መሆኑን መጻሕፍት ይመሰክሩለታል። መንፈሳዊ ሕይወቱን ሢመት ያላደበዘዘበት፣ በዘመኑ ከተነሣ ኑፋቄ ጋር ሲጋደል የኖረ አባት ነው። በጣም መንፈሳዊ በመሆኑም አምላኩን በጸሎት ጠይቆ ሊሞት ለነበረ አንድ ካህን ዕድሜ እንዲጨምርለት አድርጓል። እንደ ኢያሱ ፀሐይ ከመግባት እንድትዘገይ አድርጓል (ድርሳነ ቄርሎስ ገጽ፣ ፫-፭)። ቅዱስ ቄርሎስ መናፍቃንን ቀጥቅጦ የሚያደቅ መዶሻ መሆኑን የምትመሰክረው ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ብቻ ሳትሆን ፈላስፎች ጭምር መሆናችን በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የዶግማ መምህር የነበሩት ቀሲስ ዶክተር ዮሴፍ ያዕቆብ ክፍል ውስጥ ደጋግመው ይናገሩ ነበር።
በፎክሎርና ሥነ ጽሑፍ ትምህርት ክፍል “ዘመን አይሽሬ የግእዝ ሥነ ጽሑፍ” የተሰኘውን ትምህርት ለማስተርስ ተማሪዎች ያስተምሩ የነበሩት ዶክተር ዮናስ አድማሱ የቅዱሱን ድርሰት ለማስተማሪያ እንዲሆን አባዝተው ለተማሪዎቻቸው ይሰጧቸው ነበር። ቅዱስ ቄርሎስን ያሳደገው የእናቱ ወንድም አጎቱ ቅዱስ ቴዎፍሎስ ዘእስክንድርያ ነው። መንፈሳዊ ትምህርትን ከተግባራዊ ክርስትና ጋር እየተማረ ያደገው በእስክንድርያ መንበረ ፕትርክና ውስጥ ነው። አጎቱ ቅዱስ ቴዎፍሎስ ከዚህ ዓለም ድካም ሲያርፍ በየሀገረ ስብከቱ የነበሩ ጳጳሳትና የእስክንድርያ ክርስቲያኖች ፓትርያርክ እንዲሆን መርጠው አሾሙት።
ቅዱሱ አባት መንፈሳዊ ዕውቀት፣ ከጽኑ መንፈሳዊ ተጋድሎ ጋር የሠመረለት፣ ሃይማኖት ከምግባር ጋር የተዋሐደለት ነበር። እርሱ የእስክንድርያ ፓትርያርክ በሆነበት ዘመን ንስጥሮስም በቍስጥንጥንያ መንበር ላይ ፓትርያርክ ሆኖ ተሾመ። መናፍቃን ሹመት ሲያገኙ ደብቀውት የኖሩትን ኑፋቄ ማውጣት መገለጫቸው በመሆኑ ንስጥሮስም ሲሾም በድርያድርስ ተጽፎ ዕቃ ቤት የነበረን ጽሑፍ አግኝቶ በማንበብ “ደግ ሃይማኖት ነው” ብሎ በውስጡ ደብቆት የኖረውን ኑፋቄ በገሀድ ማስተማር ጀመረ። መናፍቃን ሹመት ሲያገኙ ደብቀውት የኖሩትን ኑፋቄ የሚያወጡት አንድም ሥልጣን ስለያዝን ማን ይነካናል በማለት ሲሆን ሁለትም እነርሱን ያህል አባቶች ጥቅም ባያገኙበት ኖሮ ሃይማኖታቸውን በቀላሉ አይቀይሩም ነበር በማለት የዋሃን እንዲከተሏቸው በማሰብ ነው።
የንስጥሮስን ድርጊት የሰማው ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ ድርጊቱን የፈጸመው ራሱ ንስጥሮስ መሆኑን ዕያወቀ ሌላ ሰው የፈጸመው አስመስሎ እንዲህ ያለ ክሕደት የሚያስተምር ሰው በሀገረ ስብከትህ አለና መርምር ብሎ ይልክበታል። ንስጥሮስም በሀገረ ስብከቴ አንተ ያልከውን አይነት ኑፋቄ የሚያስተምር ሰው የለም ብሎ መልሶ ይልክበታል። ትንሽ ቆይቶ እንደ ገና እንዲህ ያለ ኑፋቄ የሚያስተምር ሰው በሀገረ ስብከትህ አለና አጣራ ብሎ ይልክበታል። እርሱ ግን የለም ብሎ መልስ ሰጥቶ ኑፋቄውን በዐደባባይ ማስተማሩን ይቀጥላል።
ሦስተኛም ሲልክበት ከእርሱ ኑፋቄ ይከፋል ብሎ ያሰባቸውን መናፍቃን ስም ጠርቶ እኔ እንደ እነርሱ አላስተማርኩም። አንተ የጠቀስከውን አይነት ትምህርት ባስተምር ምንድን ነው ጥፋቴ አይነት መልስ ይሰጠዋል። ቅዱሱ አባት እንደ ገና በዘመኑ የምሥራቅ ሮማ ግዛት ንጉሥ ወደ ነበረው ወደ ታናሹ ወይም ዳግማዊ ቴዎዶስዮስ እንዲህ ያለ ኑፋቄ የሚያስተምር ሰው በግዛትህ አለና አጣራ ብሎ ይልክበታል። መልእክቱንም ለንጉሡ ብቻ ሳይሆን በንጉሡ ላይ ጫና እንዲያሳድሩ ለንጉሡ እኅትና ለልጁ ይልክላቸዋል።
ጉዳዩን አጣርቶ የደረሰበት ዳግማዊ ቴዎዶስዮስም ቅዱስ ቄርሎስን አባቴ ያልከው ትክክል ነው። ንስጥሮስ የጠቀስኸውን ኑፋቄ በማስተማር ላይ ነው ብሎ ነገረው። በመቀጠልም አባቴ ጉባኤ ልጥራልህና ተከራከሩ አለው። ቅዱሱ አባትም በንጉሡ አሳብ ተስማማ። በዚህ ምክንያት በ፬፴፩ በቍስጥንጥን ጉባኤ ተደረገ። ቅዱስ ቄርሎስ ጉባኤ ወደ ተጠራበት ቍስጥንጥንያ ሲሄድ ጳጳሳትን ብቻ ሳይሆን የገዳም አባቶችን ጭምር ይዞ ነበር የሄደው። ቅዱሱ እንዲህ ያደረገበት ምክንያት በበረሃ በተጋድሎ የሚኖሩ አባቶች በጸሎት እንዲያግረዙት ሲሆን ከዚህ በተጨማሪም ከመካከላቸው ለፓትርያርክነትም ሆነ ለጵጵስና የሚያበቃቸው አባቶች ቢኖሩ በጉባኤ መልስ መስጠት እንዲማሩ በማሰብ ነበር።
ቅዱስ ቄርሎስ ይዟቸው ከሄዳቸው ገዳማውያን አባቶች አንዱ ከመንፈሳዊ ብቃቱ የተነሣ ደመና ጠቅሶ ይጓዝ እንደ ነበር ከመጋቢት እስከ ጷግሜን የሚነበበው መጽሐፈ ስንክሳር ያስነብበናል። የቅዱሱ አባት መንፈሳዊ ብቃትም ከጉባኤ ቍስጥንጥንያ በኋላ ተፈጽሞ ታይቷል። ይኸውም ጉባኤው ተጠናቆ ሁሉም ወደየመጣበት ሲመለስ ቅዱሱ አባት ለብሶት የነበረው በጣም የተበጣተሰ ልብስ መሆኑን የተመለከቱ መርከበኞች ቆሻሻ ልብስ ለብሰህ ከታላላቅ አባቶች ጋር መሄድ አትችልም ብለው በመርከብ ከመሳፈር አስቀሩት። መርከበኞቹ የፈጸሙትን ድርጊት ቅዱስ ቄርሎስ አላወቀም ነበር። ፓትርያርኩ የተሳፈረባት መርከብ ከባሕሩ መሐል ስትደርስ በመርከብ እንዳይሳፈር የተከለከለው አባት በደመና ተጭኖ በመርከቧ አናት ላይ ሲያልፍ የተመለከተው ቅዱስ ቄርሎስ አባቴ በጸሎት አስበኝ በማለት ተማጸነው። በሌላ በኩል ማለፍ ሲችል እግዚአብሔር ይህን ያደረገው መርከበኞቹ እንዲያምኑ ነበር። ያም አባት ዕለቱን ከገዳሙ ገብቶ ከመነኰሳት ጋር በጸሎት ተሳትፏል።
በንጉሡ አሳብ አቅራቢነት ለተጠራው ጉባኤ ሊቀ መንበሩ ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ ነበር። ቅዱሱ አባት ንስጥሮስን መልስ አሳጥቶ ከረታው በኋላ ወደ አማናዊቷ ሃይማኖት እንዲመለስ አባቶች ቢለምኑትም ንስጥሮስ ግን ፈቃደኛ ሳይሆን ቀረ። በዚህ ምክንያትም ንስጥሮስ ወደ ላዕላይ ግብፅ ተጋዘ (ድርሳነ ቄርሎስ በሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ሐዲስ፣ ገጽ ፫-፭)። መናፍቁ ንስጥሮስ በላዕላይ ግብፅ ከተጋዘ በኋላም ቢሆን ቅዱስ ቄርሎስ ደጋግሞ “እመቤታችንን ወላዲተ አምላክ፣ ጌታችንን መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ደግሞ አምላክ ወሰብእ” ብሎ እንዲያምን ከልመና ጋር መልእክት ይልክበት ነበር። ንስጥሮስ ግን “የያዝኩት ተስማምቶኛል አልመለስም” ብሎ በክሕደቱ ቀጠለ።
ቅዱስ ቄርሎስ ንስጥሮስን ብዙ ጊዜ ለምኖት ለመመለስ ፈቃደኛ ባለመሆኑ “እመቤታችንን ወላዲተ አምላክ፣ ጌታችንን መድኃኒታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ደግሞ አምላክ ወሰብእ” ብላ ለማመን ፈቃደኛ ያልሆነች ምላስህ አትታዘዝልህ በማለት ረገመው። ወዲያውም የንስጥሮስ ምላስ ተጎልጉሎ ደምና መግል ይወጣው ጀመር። በዚህ ሁኔታ ሲሠቃይ ኖሮ ንስጥሮስ ይህን ዓለም ተሰናበተ። በደዌ በመሠቃየቱ ይህን ዓለም፣ ከአምላኩ በመለየቱት የወዲያኛውን ዓለም አጣ። የመንፈሳውያን አባቶች ጸሎታቸው እንደሚጠቅም ሁሉ ውግዘታቸው ቆርጦ የሚጥል ሰይፍ መሆኑን ከቅዱስ ቄርሎስና ከንስጥሮስ ታሪክ እንረዳለን።
በዘመናችን ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን የሚመሩ አባቶችም እንደ ቅዱስ ቄርሎስ ቢሆኑ አገር ትጠቀማለች። በዚህ ዘመን ፈልጋ መሾም የሚገባትም እንደ እርሱ ያሉትን አባቶች ነው። ቅዱስ ቄርሎስን የመሰሉ አባቶችን ማግኘት የሚቻለው ከልሂቅ እስከ ደቂቅ ክርስቲያኖች ሁሉ ጸሎት በመያዝ አምላካቸውን እንዲማጸኑ በማድረግ ነው። እኛ ከለመንነው “ለምኑ ይሰጣችኋል” ብሎ ቃል የገባልን አምላክ የፈቀድነውን ሊሰጠን የታመነ ነው።

“ልባችሁ በጸጋ ቢጸና መልካም ነው እንጂ በመብል አይደለም” ዕብ. ፲፫፡፱

“ልባችሁ በጸጋ ቢጸና መልካም ነው እንጂ በመብል አይደለም” ዕብ. ፲፫፡፱

“ልባችሁ በጸጋ ቢጸና መልካም ነው እንጂ በመብል አይደለም” ዕብ. ፲፫፡፱

“ልባችሁ በጸጋ ቢጸና መልካም ነው እንጂ በመብል አይደለም” ዕብ. ፲፫፡፱

በቅርቡ የመስኖ ፕሮጀክት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ጉዳዩ ጋር ግንኙነት የሌለውን ጥናት በመጥቀስ በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው የሚከተለውን ጽሑፍ አጋርተዋል።

በግርድፉ ወደ አማርኛ ሲመለስ “ጤናማ አመጋገብ፣ የምግብ ብዝኀነት እና የምግብ ዋስትና ማኅበራዊ ጤናን፣ የሥራ ምርታማነትን፣ ጤናማ ሰብአዊ ግንኙነትን፣ ሰላምና የኢኮኖሚ ዕድገትን ለማምጣት ቁልፍ ሒደቶች ናቸው። የኢትዮጵያ አመጋገብ ባህል (በተለይም የሰሜን ኢትዮጵያ) በሃይማኖት ተጽፅኖ ሥር የወደቀ ስለሆነ ጤናማ ላልሆነ አመጋገብ አጋላጭ ነው። እነዚህ ችግሮች ካልተፈቱ ወደ ብልጽግና፣ ሰላም እና መረጋጋት የሚደረገው ጉዞ ዘላቂነት አይኖረውም። ጤናማ ያልሆነ አመጋገብ የሚያቃውሰው የግለሰብ ጤናን ብቻ አይደለም። ኃይልን ያዳክማል፤ ፖለቲካዊ ውሳኔዎችን ጨምሮ ውሳኔ መስጠት ላይ ተጽዕኖ ያሳድራል፣ ከሌሎች ሰዎች ጋር ያለን ግንኙነትን ያዛባል፤ ግጭቶችን ያመጣል” የሚል ነው። ይህ ስም ማጥፋት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ በግልጽ ከተቃጡ የአሳብ ጦርነቶች አንዱ ነው።

በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ አካላት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ የተለያዩ ስም ማጥፋቶችን ሲፈጽሙ ቆይተዋል። አንዳንዶቹ በዓላትን በማብዛት ለብሔራዊ ድኅነት ተጠያቂ ያደርጓታል፤ ሌሎች ለቅዱሳን ዝክር፣ ለሙታን ተዝካር ሀብት ንብረት በማባከን ይወቅሷታል፤ እነዚህ ደግሞ ጾም በማብዛት ሰዎች ጤናቸው እና የማሰብ ችሎታቸው እንዲቀንስ እንዳደረገች እየከሰሷት ይገኛሉ። ቤተ ክርስቲያን ግን ከእነዚህ ሁሉ ክሶች ነፃ ናት። ሆድን የፈጠረ እግዚአብሔር ለሰው ልጅ ምግብ እንደሚስፈልገው፣ እንዳዘጋጀለትም ታምናለች፣ ታውቃለች፤ ታስተምርማለች። ምግብ መብላትንም አትቃወምም። ነገር ግን “ሁሉ በአግባብና በሥርዓት ይሁን” በሚለው ክርስቲያናዊ አስተምህሮዋ ልጆቿ ለመኖር እንዲመገቡ እንጂ ለመብላት እንዲኖሩ አትፈቅድም። እንዲህ ያለው መፈክር ለመብል ብቻ ለተፈጠርን ለሚመስላቸው ነው። ምግብ ለሰው ልጅ ኑሮ አስፈላጊ ቢሆንም ሰው የተፈጠረው ከመብልና ከመጠጥ ላለፈ ዓላማ መሆኑን ዕለት ዕለት ትሰብካለች። የቤተ ክርስቲያንን አስተምህሮ ሳይንስ ስለደገፈው እውነት፣ ስላልደገፈው ደግሞ ሐሰት የሚባል አለመሆኑን መረዳት ይገባል።  ተመራማሪዎች ጾም አስፈላጊ ስለመሆኑ፣ የሚጾሙ ሰዎች ከማይጾሙ ሰዎች ይልቅ የተረጋጉ፣ የልብና የስኳር መጠናቸውን በመጠበቅ የተሻለ ጤና ያላቸው ስለመሆናቸውና ረጅም ዕድሜ የሚኖሩ እንደሆኑ በጥናት ማረጋገጣቸውን እየመሰከሩ ባለበት ወቅት ሥልጣንን መከታ አድርጎ ጥላቻን መዝራት ተገቢ አለመሆኑን ማስገንዘብ እንወዳለን። የሰሞነኛ ክስ ምንጩ ሰበብ እየፈለጉ ኦርቶዶክሳውያንን እና ለሆዳቸው አለመፈጠራቸውን የሚያምኑትን ማሸማቀቅ ነው።

ምኞታቸውን በማኅበራዊ ብዙኃን መገናኛ ያካፈሉት ባለሥልጣን ከልጥፉ ጋር አንድ ጥናት ያያያዙ ቢሆንም ጥናቱ እርሳቸው ስለሚሉት ጉዳይ የሚጠቅሰው ነገር የለም። ጥናቱ የተሠራው በራሳቸው እና  በሌሎች ሁለት ግለሰቦች የተደረገው ጥናት “Smallholder milk market participation, dietary diversity and nutritional status among young children in Ethiopia” የሚል፣ ትኩረቱም በወተት ተጠቃሚዎች ላይ ነው። እርሳቸው ያለ ዐውዱ ቢጠቅሱትም ከተባለው ጉዳይ ጋር ፈጽሞ ግንኙነት የለውም። ደግሞስ ጾም የሚጾሙ በአብዛኛው ከዐሥር ዐመት በላይ የሆኑ ሰዎች ናቸው። ሕፃናት ከእንስሳት ተዋጽዖ አይከለከሉም። የተመጣጠነ ምግብ መመገብም በሃይማኖት የተከለከለ አይደለም። ስለሆነም አቅርቦቱ በሌለበት፣ ብዙዎቹ ከእጅ ወደ አፍ ኑሮ እየገፉ የሚበሉት አትተው በሚሰቃዩበት አገር የተመጣጠነ ምግብ የማይመገቡት በሃይማኖቱ እንሌመገቡ ስለተከለከሉ ነው የሚል አሳብ ማቅረብ ሃይማኖቱን መጥላት፤ ሕዝብንም መናቅ ነው። ባለሥልጣኑ ሃይማኖትን ለመንቀፍና ቤተ ክርስቲያንን ለመውቀስ ብቻ የራስን አሳብ ያለ ማስረጃና ማረጋገጫ እንደ ተጨባጭ እውነት ማቅረባቸው በእጅጉ የሚያስነቅፍ ነው።

በቅዱሳን መጻሕፍት ብዙ ቅዱሳን ያለ ምግብ ወይም መናኛ ምግብ በመመገብ አገርንም ቤተ ክርስቲያንንም በሰላም ሲመሩ ኖረዋል። እንዲያውም ክርስትና ከድሎትና ከምቾት ጋር ስምም አይደለም። ከቅዱሳን ሐዋርያት ጀምሮ ሐዋርያውያን አበው፣ ዐቃብያነ እምነት፣ ቅዱሳን ሊቃውንት፣ ቅዱሳን ሰማዕታት እና ቅዱሳን ጻድቃን አልጫን ዐለም በቅድስና ሕይወታቸው ያጣፈጡት የላመ የጣመ እየበሉ አይደለም። በብሉይ ኪዳንም በ፳፯ አገሮች ላይ የተሾመው ነቢዩ ዳንኤል ይህን የመሪነት ሥራውን ያከናውን የነበረው “ሐሰተኛ ምሁራን” እንደሚሉት የተመጣጠነ ምግብ እየተመገበ ሳይሆን የንጉሡ ምግብ እንዳያረክሰው በማሰብ ቆሎ እየቆረጠመ ነበር። ለዐሥር ቀን ቆሎ እየቀመሱ የሰነበቱት ሠለስቱ ደቂቅ ንጉሡ እንዲመገቡ ካዘዘው  ይመገቡ ከነበሩት አምሮባቸውም፣ በአእምሮ ልቀውም መገኘታቸው ጤና የሚጠበቀው በምግብ ሳይሆን ምግብን በፈጠረ እግዚአብሔር መሆኑን የሚያስገነዝብ ነው።

ጌታችን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በገዳመ ቆሮንቶስ ከቆመበት ሳያርፍ፣ ከዘረጋበት ሳያጥፍ ለአርባ ቀናት መጾሙ፣ ስንጾምም እንዴት መጾም እንዳለብን ማስተማሩ ጾም ለሰው ልጆች አስፈላጊ መሆኑን መግለጹ ነው። በኦርቶዶክሳውያን ዘንድ የጾም አስፈላጊነት ክርክር የማይነሣበት ዶግማ ነው። የሰይጣንን ፈተና ድል ለመንሣትም ዋና መሣሪያችን መሆኑን ሁልጊዜ ስለ ምግብ እንድናስብ በማድረግ፣ በመብል ሊጥለን የሚፈልግ ዲያብሎስ የመብል ፈተና ሲያቀርብለት “ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ አይኖርም፤ ተብሎ ተጽፏል” (ማቴ. ፬፡፬) በማለት አሳፍሮ አሳይቶናል። ስለሆነም ስለ ምግብና ስለ ሆድ ማሰብ ሞት ነው። እንዲያውም ሆድ በሞላ ቁጥር አእምሮ የማሰብ አቅሙ እየቀነሰ ይሔዳል። አብዛኛዎቹ የዐለም ፈጠራዎች ችግርና ማጣት የወለዳቸው ናቸው። ሰው ሁሉም ነገር ከተሟላለት የማሰብም ሆነ የመሥራት ፍላጎት አይኖረውም።

የኢትዮጵያ አብዛኛው ሕዝብ ባለሥልጣናቱ እንደሚያወሩት የተመጣጣነ ምግብ የሚያውቅ፣ በቀን ሦስት ጊዜ የሚመገብ አይደለም። ነገር ግን ከሌሎች ጋር ተሳስቦና ተግባብቶ የመኖር ችግር የለበትም። የማሰብም ሆነ ውሳኔ የመስጠት ጉድለት የለበትም። እንዲያውም በተቃራኒው መርጠው የሚመገቡትና በተመጣጠነ ምግብ ሰበብ መብልን ሥራቸው ያደረጉ ሹማምንት የሚሰጡት ውሳኔ ነው አገር ሲያጠፋ የሚታየው። የሚመሩትን ሕዝብ ማወቅ፣ ያለበትንም የኑሮ ደረጃ መገንዘብ ብዙ ከመሳት ይጠብቃል። የአገር ዕድገት በመሪዎች ሀብትና ቅንጡ አኗኗር አይመዘንም። በኢትዮጵያ የተመጣጠነ ምግብ ያለው ትምህርት ቤት ከመምህራን አፍ፣ በቴሌቪዥን መስኮት ከዝግጅት አቅራቢዎች እና በዐደባባይ ከባለሥልጣናት ንግግር ብቻ ነው። በገጠሩ የሚኖረው ማኅበረሰብ ባለማግኘት፣ ያለውም ቢሆን ከመብል ጋር ያለው አስተሳሰብ ከመኖር ጋር ብቻ የተያያዘ ስለሆነ ስለ ተመጣጠነ ምግብ ጉዳዩ አድርጎ አያስብም፤ አይበላምም። ይህ የተሠራበት እሴት በሕይወቱ ላይ ያመጣበት ችግር የለም። ጾሙንም እንደ ጫና ሳይሆን እንደ በረከት የሚቆጥረው ተረድቶት ነው። ቤተ ክርስቲያን ያለ ጥናት እንደሚናገሩት አካላት የተመጣጣነ ምግብ መመገብን አትከለክልም። ማግበስበስን ግን ትጸየፋለች።

ይህን የምታስተምረው ደግሞ እንደ እንግዳ ደራሽ፣ እንደ ውኃ ፈሳሽ መሠረት የሌለው ሳይሆን ከአምላኳ የተቀበለችው፣ ከሐዋርያት የተረከበችው ነው። ጌታችን በወንጌል “ለሚጠፋ መብል አትሥሩ፤ ነገር ግን ለዘላለም ሕይወት ለሚኖር መብል የሰው ልጅ ለሚሰጣችሁ ሥሩ” (ዮሐ. ፮፡፳፯) በማለት ሰው ሊሠራ የሚገባው አላፊ ለሆነው ዐለም ምግብ ብቻ ሳይሆን የዘላለም ሕይወቱን እያሰበ እንዲኖር ነው። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስም “መብል ለሆድ ነው፤ ሆድም ለመብል ነው፤ እግዚአብሔር ግን ይህንም ያንም ያጠፋቸዋል” (፩ኛ ቆሮ. ፰፡፰) በማለት ሆድም መብልም እንደሚጠፉ ነግሮናል። አብዝቶ መብላት መጠጣት ወደ ጥጋብና እግዚአብሔርን ወደ መርሳት ያደርሳል። “ይሹሩ ወፈረ፣ ረገጠ፤ ወፈረ፣ ደነደነ፣ ሰባ፤ የፈጠረውንም እግዚአብሔር ተወ፤ የመድኀኒቱንም አምላክ ናቀ” (ዘዳ. ፴፪፡፲፭) የሚለው የመጽሐፍ ቃል የሚያስረዳን ይህኑ ነው። ስለሆነም ስለ ሥጋ ማሰብ፣ ስለ መብልና መጠጥ ብቻ ማስብ “ሊበሉና ሊጠጡ ተቀመጡ፣ ሊዘፍኑ ተነሡ” (፩ኛ ቆሮ. ፲፡፯) ተብሎ እንደተጻፈ እግዚአብሔርን መርሳትና ሞት ነው።

በመንፈስ ቅዱስ የተቃኙ አባቶች

በመንፈስ ቅዱስ የተቃኙ አባቶች

በመንፈስ ቅዱስ የተቃኙ አባቶች

በመንፈስ ቅዱስ የተቃኙ አባቶች

የመንፈስ ቅዱስ መሰንቆ የቃኛቸው አባቶች በመንፈሳዊ ሥልጣን ላይ ሲቀመጡ ራሳቸውንም ሌሎችንም ይጠቅማሉ። በመንፈስ ቅዱስ የተቃኙ አባቶች በፈቃደ እግዚአብሔር ስለሚመሩ ክርስቲያኖች ሁሉ እግዚአብሔር በሚፈቅደው መንገድ እንዲጓዙ ያደርጋሉ። እንዲህ ማድረጋቸው ሃይማኖት እንዲጸና ቀኖና ቤተ ክርስቲያን እንዲጠበቅ ሳይታክቱ ይሠራሉ። መሥራት ብቻ ሳይሆን ራሳቸው አርአያ ሆነው ፈጽመው ያሳያሉ። Read more