የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት - በኢ/ኦ/ተ/ቤ የመንበረ ፓትርያርክ ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ አንድነቱ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ተቋማዊ ራእይ፣ ተልእኮ
      • መዋቅራዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቋማዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማስፈጸሚያ
    • ስልታዊ እቅድ 2018 – 2021 ዓ/ም
  • ሥርዓተ ትምህርት
    • መሠረታዊ መረጃዎች
    • የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት አደረጃጀት መመሪያ
    • የሥርዓተ ትምህርቱ መመማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
    • የሥርዓተ ትምህርቱ ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ /ካሌንደር
    • የመምህራን ሥልጠና እና መልእክቶች
    • መጻሕፍቱን ለማግኘት እና ተጨማሪ መረጃ
    • ልዩ ልዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች
  • ፕሮጀክቶች
  • መዝሙረ ማኅሌት
    • የመስከረም ወር መዝሙሮች
      • የዮሐንስ መዝሙር
      • የመስቀል መዝሙሮች
      • የብዙኃን ማርያም መዝሙር (መስከረም ፳፩ )
      • የዘመነ ጽጌ መዝሙር
    • የጥቅምት ወር መዝሙሮች
      • የአብርሃ ወአጽብሐ መዝሙር (ጥቅምት 4 ቀን)
    • የኅዳር ወር መዝሙሮች
      • የቅዱስ ሚካኤል መዝሙር (ኅዳር 12 ቀን)
    • የጥር ወር መዝሙሮች
      • የዘመነ ጥምቀት መዝሙር
      • የቃና ዘገሊላ መዝሙር (ጥር 12 ቀን)
    • የመጋቢት ወር መዝሙሮች
      • የወርኃ ጾም መዝሙሮች
      • የሆሣዕና መዝሙራት
      • የሰሙነ ሕማማት መዝሙሮች
  • ዜና
    • አጫጭር ዜናዎች
    • ዝርዝር ዜናዎች
    • ወቅታዊ መረጃዎች
    • ማስታወቂያ
      • የሰንበት ትምህርት ቤቶች መጻሕፍት እንግሊዝኛ ትርጉም ሥራ ተሳትፎ ጥሪ
  • ያግኙን
  • ቋንቋ
    • ትግርኛ
    • Afaanoromo
  • Menu Menu

ነፋስን ዘርተዋል፤ ዐውሎ ነፋስንም ያጭዳሉ (ሆሴ. ፰፡፯)

ነፋስን ዘርተዋል፤ ዐውሎ ነፋስንም ያጭዳሉ (ሆሴ. ፰፡፯)

ነፋስን ዘርተዋል፤ ዐውሎ ነፋስንም ያጭዳሉ (ሆሴ. ፰፡፯)

ቸርነት የባሕርይ ገንዘቡ የሆነው አምላካችን እግዚአብሔር “ብትወዱኝስ ትእዛዜን ጠብቁ” ብሏል። ትእዛዛቱን በመጠበቅ የሚገኘው ክብር ደግሞ የዘለዓለም ሕይወት መሆኑን ገልጾልናል። የምንጠብቃቸውን ትእዛዛት በተመለከተ ደግሞ አንድ ሕግ ዐዋቂ “ከሕግ ማናቸይቱ ትእዛዝ ትልቅ ናት?” ብሎ በጠየቀው ጊዜ ጌታ የሰጠው መልስ “አምላክህን በፍጹም ልብህ፣ በፍጹም ነፍስህ፣ በፍጹም አሳብህ ውደድ። ታላቂቱ እና ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት። ሁለተኛይቱም ይህችን ትመስላለች። እርስዋም ባልንጀራህን እንደ ነፍስህ ውደድ የምትለው ናት። በእነዚህ በሁለቱ ትእዛዛት ሕግም ሁሉ ነቢያትም ተሰቅለዋል” (ማቱ. ፳፪፡፴-፮፵) የሚል ነው። ከእነዚህ ከሁለቱ ትእዛዛት የሚወጣ ሕግ እና ትእዛዝ የለም። ሁሉም ሕግጋት ፍቅረ እግዚአብሔርን እና ፍቅረ ቢጽን መሠረት ያደረጉ ናቸው። እነዚህን ትእዛዛት ማክበር በምድር ላይ ሰላምን ይሰጣል፤ ዕድሜን ያረዝማል፤ በሰማይ የዘለዓለም ሕይወትን ያስገኛል።
የእግዚአብሔርን ትእዛዝ መጠበቅ ምድራዊ ጸጋ ሰማያዊ ዋጋ ያለው እንጂ እንዲሁ በከንቱ የሚደረግ አይደለም። በምድር ላይ ግን ለሕግ ካለመታዘዝ ጀምሮ ዐመጽ፣ ጠብ፣ ክርክር፣ አድማ፣ ሁከት እና ራስ ወዳድነት ተንሰራፍቶ ታያል። እንዲህ ያለው መጥፎ ጠባይ በማያምኑት መካከል ብቻ ሳይሆን እናምናለን በሚሉት እና የእግዚአብሔርን ቃል ዕለት በዕለት በሚሰብኩትም መካከል ያለ እንክርዳድ ነው። አልጫውን ዐለም ጨው ሆነው ያጣፈጡ የሐዋርያት ልጆች፣ ብርሃን ሆነው ያለማወቅን ጨለማ የገፈፉ የቅዱሳን ሊቃውንት ተከታዮች፣ ሁሉን ትተው አምላካቸውን የተከተሉ ቅዱሳን ጻድቃን ወዳጆች፣ ስለ ስሙ የተሰደዱና ስለ ስሙ የተገደሉ ቅዱሳን ሰማዕታት ልጆች ለዐለሙ የሚተርፍ ቀርቶ ለራሳቸው የሚሆን ሰላም ከሌላቸው ክርስትናን ከመግደል አይተናነስም።
ፍቅር ሒደት ሲሆን ውጤቱ ደስታና ሰላም ነው። ሰው እግዚአብሔርን እና ሰውን ከወደደ በእግዚአብሔር ላይ ኃጢአት፣ በሰው ላይ ክፋት ስለማይሠራ ዐለም ሰላም፣ ሕይወትም በደስታ የተሞላች መሆኗ የታመነ ነው። ነገር ግን በዐለም ላይ በተለይም በአገራችን የምናየው ከዚህ በተቃራኒ ነው። የፍቅር መቀዛቀዝ፣ የመንፈስ ዝለት፣ አድመኝነት እና መለያየት ተንሰራፍቷል። የሰላም ዋጋ ቀንሷል። የእብድ ገላጋይ በዝቷል። በለው፣ ፍለጠው፣ ቁረጠው እንጂ ተዉ የሚል ጠፍቷል። አስታራቂ ሽማግሌ፣ ሰሚ ልጅም የለም። በዚህም ምክንያት ሰው ስለ ክፋት ሲያስብ፣ ሰውን ስለ ማጥቃት ሲያሰላስል ያድራል። ወንድም በወንድሙ ላይ፣ ወገን በወገኑ ላይ፣ ሕዝብ በሕዝብ ላይ ተነሥቷል። “ከባል የታመነ ከማን ጋር ይሔዷል?” እንዳልነበረ ተረቱ መንግሥትም የሕዝብን ሰላም መጠበቅ ኃላፊነቱ መሆኑን ዘንግቷል። በዚህም ምክንያት እንደ አገር አመጽ ነግሦ ሰዎች ያለመኖር ስጋት ውስጥ ይገኛሉ። ሌሎች ሊያጠቁኝ ነው ብሎ የሚያስብ አካል ደግሞ ራሱን ለመከላከል መነሣቱ ተፈጥሯዊ ነው። በዚህ ምክንያት ሽግግራችን ከጦርነት ወደ ጦርነት ሆኗል። የጦርነትን አስከፊነት የሚናገሩ አንደበቶች ብዙ ቢሆኑም በገቢር ጦርነትን ለማስቆምና ሰላምን ለማምጣት የሚሠሩ ግን ጥቂት ናቸው ወይም የሉም።
በአገራችን የሚከሠቱ አብዛኛዎቹ ችግሮች ቅንነት ማጣት የወለዳቸው ናቸው። ለሚጠየቁ ጥያቄዎች፣ ለሚፈጸሙ ጥቃቶች፣ ለሚደርሱ ጉዳቶች ተገቢውን መልስ ከመስጠት፣ ጥበቃ ከማድረግ እና ከመከላከል ይልቅ ቸል ማለት እና ኃላፊነትን መዘንጋት ብሎም ለአጥፊዎች ከለላ መስጠት ጎልቶ ይታያል። አገራዊ ዕሴቶችን ማቃለል፣ የሃይማኖት አባቶችን እና የአገር ሽማግሌዎችን ለተገቢው ሰላም ሳይሆን ለፖለቲካ ትርፍ ለመጠቀም ጥረት ይደረጋል። ይህ ዐይነቱ አካሔድ በጊዜው ካልታረመ አገርን ለከፋ ችግር በማጋለጥ ወደ መጥፎ አዘቅት ያወርዳል።
አገር የምትድነው በጥቂት ቅኖች ነው። በቅንነት አገር ለማቅናትና ሰላም ለማምጣት የሚተጉትን መግፋት ብሎም አገልግሎታቸውን ማጣጣል ጉዳቱ ለራሳቸው ለአጣጣዮቹ ነው። በጦርነት ላይ ያሉ ወገኖች ቆም ብለው ሊያጤኑት የሚገባው ጉዳይ አገርን በማስቀደም ሳይሆን በክፋት እና በተንኮል ጥቃት የሚፈጽሙ አወዳደቃቸው የከፋ መሆኑን ነው። ጠቢቡ ሰለሞን “የሰው አካሔድ እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘው እንደ ሆነ በእርሱ እና በጠላቶቹ መካከል ስንኳ ሰላምን ያደርጋል” (ምሳ. ፲፮፡፯) ይላል። ስለሆነም ሁል ጊዜም ሰው የሚሔድበት የክፋት ወይም የቅንነት መንገድ መሆኑን ሊያስተውል ይገባል። በእልህ፣ በማን አለብኝነት እና በክፋት መንገድ ከመሔድ መቆጠብ ያስፈልጋል። ሰው የሌላውን መብትና ጥቅም በመጋፋት፣ ሌላውን ለመደበል በማሰብ የሚፈጽመው ተንኮል የሚጎዳው ራሱን ነው። ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት “ኀጢአተኞችን ክፋታቸው ይገድላቸዋል” እንዳለ በጠማማነት የሚጓዙ መጨረሻቸው ውድቀትና ሞት ነው። “በዋጋ ተገዝታችኋልና የሰዎች ባሪያዎች አትሁኑ” (፩ና ቆሮ. ፯፡፳፫) የተባሉትን ክርስቲያኖችን በኃይል ለመግዛት፣ በጉልበት ለማጥፋት በራሳቸው የሚመኩ ሁሉ ወደ ልቡናቸው ሊመለሱ ይገባል። ይህን ባያደርጉም እግዚአብሔር የምሕረት አምላክ ነውና የልጆቹን ነፍስ ይጠብቃል፤ ከጠላቶቻቸውም እጅ ያድናቸዋል። “የጻድቃን መከራቸው ብዙ ነው፤ እግዚአብሔር ከሁሉ ያድናቸዋል፤ አጥንቶቻቸውንም ይጠብቃል፤ ከእነርሱም አንድ አይሰበርም” (መዝ. ፴፫፡፲፱) የተባለው የሚገጥማቸው መከራ ብዙ ቢሆንም እግዚአብሔር ከመከራ ስለሚያድናቸው ነው።
በሰዎች ላይ ክፋትን የሚያደርጉ ግን በቆፈሩት ጉድጓድ ይገባሉ። “ጉድጓድ የሚምስ ይወድቅበታል፤ ቅጥርን የሚያፈርስ ጊንጥ ትነድፈዋለች። ድንጋይ የሚፈነቅልም ይታመምበታል፤ እንጨት የሚፈልጥ ይጎዳበታል” (መክ. ፲፡፲፰) ተብሎ ተጽፏል። “ጉድጓድ ስትቆፍር አርቀህ አትቆፍረው የሚገባበት አይታወቅምና” ተብሎ የተነገረው ያለ ምክንያት አይደለም። በተንኮል በመነሣሣት በሰዎች ላይ ክፉ ለማድረግ የሚፈልጉ ሁሉ ወደ ሰላም መንገድ ሊመጡ ይገባል። እንደ ልቤ የተባለ ዳዊት “አሕዛብ በሠሩት ጉድጓድ ወደቁ፤ በዚያች በሸሸጓት ወጥመድም ራሳቸው ተጠመዱባት” (መዝ. ፱፡፲፭) እንዳለ ክፋት የሚጎዳው ራስን ነው። የዚህን ሁሉ ማጠቃለያ ነቢዩ ሆሴዕ ገባርያነ እኪት ለክፋታቸው እጥፍ ሆኖ የክፋታቸው ዋጋ እንደሚከፈላቸው “ነፋስን ዘርተዋል፤ ዐውሎ ነፋስንም ያጭዳሉ” (ሆሴ. ፰፡፯) በማለት ገልጾልናል። ስለሆነም ከክፋታችን ልንመለስ፣ እግረ ልቡናችንን ወደ ሰላም ልናቀና እና የእግዚአብሔርን ፊት ልንፈልግ ይገባናል።
በዘመናችን የተከሠተው የሰላም መደፍረስ ሊስተካከል የሚችለው ወደ ራስ በመመለስ ስለሆነ ነፍጥ አንሥተው ሕይወት እያጠፉ ያሉ አካላት በሃይማኖት አባቶች፣ በሰብአዊ መብት ጥበቃ ተቋማት እና በሰብአዊ መብት ተሟጋች ሲቪክ ማኅበራት የሚቀርቡ የሰላም ጥሪዎችን ሰምተው ወደ ሰላም መንገድ ሊመጡ ይገባል። በተለይም መንግሥት በአገር ላይ ሰላምን የማስፈን፣ የዜጎችን ሰላም እና ደኅንት የመጠበቅ ኃላፊነት ያለበት እንደ መሆኑ መጠን ከጦርነት በመለስ ያሉ መፍትሔዎችን ሁሉ አሟጦ መጠቀም ይጠበቅበታል። በንጹሐን ላይ ጥቃት እንዳይፈጸም የመጠበቅ፣ የማስከበር እና የመከላከል ኃላፊነቱን ሊወጣ ይገባል። የሃይማኖት አባቶች እና የአገር ሽማግሌዎችም በእውነት እና በቅንነት አገራዊ ሰላም እንዲመጣ ሊሠሩ ይገባል።

አሸናፊ በሌለበት የወንድማማቾች ጦርነት የዕርቅና የሰላም መፍትሔዎችን ማዘግየት ትርፉ የንጹሐንን እልቂት ማባባስ ብቻ ነው። ይህን ደግሞ በአገራችን ከሁለት እና ሦስት ጊዜ በላይ በተግባር ተገልጦ አይተነዋል። ስለሆነም የሰላም በሮች ይከፈቱ፤ የጦርነት ጉሰማዎች ይርገቡ፣ ከጦርነት ትርፍ ለማግኘት የሚሠሩ አካላት አደብ ይግዙ። መንግሥት በይቅርባይነትና በሰላማዊ መንገድ ችግሮችን ለመፍታት ፈቃድ ያሳይ፤ ለሚጠየቁ ጥያቄዎች አግባብነት ያለው ምላሽ ይስጥ። መሪዎች ይህን ቢያደርጉ የዜጎቻቸውን ጩኸት ሰምተዋልና መንግሥታቸውን ማጽናት ይችላሉ። ይህን ባያደርጉ እግዚአብሔር የግፉዐን አምላክ ነውና የጥቃቱ ተጋላጭ የሆኑ ምስኪኖችን ጩኸታቸውን ሰምቶ ሊፈርድላቸው የታመነ ነው። ምንዱባን ሲጠሯቸው ያልሰሙና ልባቸውን እልኸኛ ያደረጉ ግን እነርሱም የሚጣሩበትና የሚጮኹበት ጊዜ ሲመጣ ሰሚ አያገኙምና ቆም ብለው ቢያስቡ መልካም ነው።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on LinkedIn
  • Share on Telegram
  • Share by Mail
https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/ትዕዛዝ.jpg 1080 1920 Abenezer Mamushet https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/logo-2-1-300x74-1.png Abenezer Mamushet2023-11-01 21:47:142023-11-01 21:47:14ነፋስን ዘርተዋል፤ ዐውሎ ነፋስንም ያጭዳሉ (ሆሴ. ፰፡፯)
Search Search

Recent Posts

  • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ
  • ሦስተኛ ዙር የ፲፪ ክፍል ምርቃት መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት ተከናወነ።

Archives

  • April 2026
  • September 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • May 2025
  • April 2025
  • October 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • July 2022
  • June 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
© Ethiopian Orthodox Church Global Sunday School Union | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
  • Link to Youtube
  • Link to Telegram
  • Link to TikTok
Link to: ጸሎታቸው የሚጠቅም ውግዘታቸው የሚጎዳ Link to: ጸሎታቸው የሚጠቅም ውግዘታቸው የሚጎዳ ጸሎታቸው የሚጠቅም ውግዘታቸው የሚጎዳ Link to: ክርስትና ከዘውግ ባሻገር የሆነ ማንነት Link to: ክርስትና ከዘውግ ባሻገር የሆነ ማንነት ክርስትና ከዘውግ ባሻገር የሆነ ማንነት
Scroll to top Scroll to top Scroll to top