‹‹እንደ ዳኛ ሳይሆን እንደ ጳጳስ አስተዳድር››

‹‹እንደ ዳኛ ሳይሆን እንደ ጳጳስ አስተዳድር››

‹‹እንደ ዳኛ ሳይሆን እንደ ጳጳስ አስተዳድር››

‹‹እንደ ዳኛ ሳይሆን እንደ ጳጳስ አስተዳድር››

ቅዱስ አምብሮስ በቅድስናቸው፣ በተጋድሏቸው ከሚጠቀሱ የምዕራብ ቤተክርስቲያን አባቶች መካከል አንዱ ነው፡፡ ገና ወደ ክርስትና ከመምጣቱ አስቀድሞ በሰሜን ኢጣልያ የምትገኘው ሜሎና የተባለች ግዛት ተሹሞ ነበር፡፡ ሹመቱን የሰማ ከእርሱ የበላይ አስተዳዳሪ የነበረ ሹም ‹‹እንደ ዳኛ ሳይሆን እንደ ጳጳስ አስተዳድር›› በማለት በመልካም ሁኔታ እንዲያስተዳድር መከረው፡፡ የዚህ ሀገረ ገዥ ምክር ገና ከኢጥሙቃን ወገን የነበረውን የአምብሮስን መጻኢ ዕጣ ፈንታ የተናገረ ትንቢት እንደ ነበር ይነገራል፡፡ እርሱም በተሾመበት ቦታ በሚያስገርም ሁኔታ፣ እጅግ በበዛ ቅንነትና ፍትሐዊነት አስተዳደረ፡፡ በሚላኖ መንበር የነበረው አርዮሳዊ ጳጳስ ሲሞት ተተኪውን በመምረጥ ሂደት በሕዝቡ መካከል ከፍተኛ ረብሻ ተነሣ፡፡ አገረ ገዥው አምብሮስ ሁከቱን ለማብረድ ሕዝቡን በሚያረጋጋበት ጊዜ አንድ ሕፃን ልጅ ድንገት ‹‹አምብሮስ ጳጳስ መሆን አለበት!›› በማለት በጩኸት ተናገረ፡፡ ሕዝቡ ተገርሞ የሕፃኑን ድምፅ የእግዚአብሔር መልእክት አድርጎ ተቀበለው፡፡ Read more

የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን

የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ታሪካችን – ክፍል ሦስት

የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን

የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን

 

ባለፉት ሁለት ተከታታይ ጽሑፎች የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ታሪካችን በፈተና የተከበበ መሆኑን አንሥተናል። ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ቅድስት ቤተክርስቲያን ከራሷ መነኰሳት ጳጳሳትን እንድትሾም ያደረጉት አስተዋጽዖ ከፍተኛ ቢሆንም በራሳቸው ወርድ ለመስፋት ያደርጉት የነበረው ጣልቃ ገብነት ደግሞ አሁን ለደረስንበት ችግር እንደ አንድ ምክንያት ሊጠቀስ የሚችል ነው።  ኢትዮጵያውያን ጳጳሳት እንዲሾሙ ያደረጉት ተጋድሎ በሌላ በኩል አባቶች መንግሥት ካከልን ብለው እንዲዘናጉ ሳያደርግ አልቀረም። በ፲፱፻፳፩ዓ.ም ከራሳችን መነኰሳት ኤጲስ ቆጶሳት እንደተሾሙ ሊቀጳጳሱና ኤጲስ ቆጶሳቱ ጉባኤ አድርገው በመምከር ሊያደርጉት የሚገባውን የሀገረ ስብከት ምደባ ንጉሠ ነገሥቱ መፈጸማቸው ለጉዳዩ ትኩረት ለመስጠት ጠቅሟል የሚል አካል ቢኖርም በየዘመናቱ ለተነሡ ባለሥልጣናት መንገድ ቀይሰዋል።

 

Read more

የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን

የኢጲስ ቆጶሳት ታሪካችን ክፍል ሁለት

የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን

የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኢጲስ ቆጶሳት ሢመት ታሪክ ውስብስብ መሆኑ የሚታወቅ ነው። ውስብስብ እንዲሆን ያደረገው በአንድ በኩል ግብፆች ሢመቱን ለጊዜያዊ ጥቅም ማግኛ በማድረግ ፓትርያርኮች ከራሳችን መነኰሳት እንድንሾም ቢፈቅዱ እንኳ የእስልምና እምነት ተከታይ መሪዎቻቸው መከልከላቸው ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ የአገራችን ነገሥታት በአዎንታዊ መንገድም ቢሆን ጣልቃ መግባታቸው “መንግሥትና ሃይማኖት የተለያዩ ናቸው” በማለት በዐደባባይ ምለው የሚገዘቱ የዘመናችን መሪዎችም በተግባር ቤተ ክርስቲያንን ለማዳከም በእጅጉ “የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ፈጻሚ” ሆነው እንዲታዩ በር የከፈተ በመሆኑ ነው። Read more

መዋቅሩ ለወንጌል ወይስ ወንጌሉ ለመዋቅሩ?

መዋቅሩ ለወንጌል ወይስ ወንጌሉ ለመዋቅሩ?

መዋቅሩ ለወንጌል ወይስ ወንጌሉ ለመዋቅሩ?

ኤፍሬም እንዳለ የተባለ ደራሲ “እንጨዋወት” በሚል ርእስ ያዘጋጀው ትኩረቱን ማኅበራዊ ሂስ ላይ ባደረገው መጽሐፍ አንድ ታሪክ እናገኛለን። ታሪኩ እንዲህ ነው። አንድ ድርጅት ከከተማ ወጣ ባለ ቦታ ያከማቻቸው አሮጌ መኪናዎች፣ የወላለቁ ብረታ ብረቶች እና ከጥቅም ውጭ የሆኑ የተለያዩ ቁሰቁሶች ነበረው፡፡ ክምችቱ ያለ ጥበቃ ለረጅም ጊዜ ቆይቷል፡፡ በኋላ ግን የድርጅቱ ባለ ሥልጣናት መጠበቅ አለበት ብለው ስላመኑ ሁለት የጥበቃ ሠራተኞች እንዲቀጠሩ ወሰኑ።

 

ከጥቂት ጊዜ በኋላ ጥበቃዎቹ በሰዓት መግባት መውጣታቸውን ከዋናው መሥሪያ ቤት ሆኖ በርቀት መከታተል እንዳልተቻለ ዘገባ ቀረበ፡፡ እነርሱን በፈረቃ የሚከታተሉ ሁለት ሰዎች ተቀጠሩ፡፡ ከቆይታ በኋላ ለአራቱ ሠራተኞች ደመወዝ ከፋይ እንደሚያስፈልግ ታመነበትና ተቀጠረ፡፡ ከዚያም የሰው ኃይል አስተዳደር መኖር አለበት ተብሎ እርሱም ተቀጠረ፡፡ የሰው ኃይል አስተዳደሩ ጸሐፊ ስላስፈለገው ጸሐፊ ተጨመረ፡፡ ይህን ሁሉ ያለ ሥራ አስኪያጅ ማስተዳደር እየከበደ ስለመጣ ዋና ሥራ አስኪያጅ ተሾመለት፡፡ እንዲህ እንዲህ እያለ ቀስ በቀስ ብዙ ሠራተኞች ያለው ድርጅት ሆነ፡፡ Read more

የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን

የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን

የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን

የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን

ኢትዮጵያውያን ከራሳችን ሊቃውንት ኤጲስ ቆጶሳት ለመሾም ያሰቡትና የጠየቁት ጥንት ነው። ከዛግዌ ነገሥታት አንዱ የሆነው ቅዱስ ሐርቤ ኢትዮጵያውያን ከራሳችን ጳጳሳት እንዲሾሙ አሳብ አቅርቦ ነገሥታት ከትምህርተ ሃይማኖትና ቀኖና ቤተ ክርስቲያን አንጻር እንዲመረምሩት አድርጎ ነበር። አሳቡ ተግባራዊ እንዲሆን የፈለገውም ጳጳስ ከግብፅ ማስመጣቱን እንደ ቅኝ ግዛት ቈጥሮት ሳይሆን ከአገራቱ ርቀት አንጻር ጳጳስ እንዲሾም የሚጠየቀው ጥያቄ ምላሽ ሳያገኝ ለብዙ ዓመታት የሚቆይ በመሆኑ፣ በዚያውም ላይ ባሕሉን የሚያውቀው፣ ቋንቋውን ከሚናገረው ቢሾም ክህነት ከመስጠት በተጨማሪ አስተምሮ ብዙዎችን መመለስ ይችላል ብሎ በማመን ነበር። Read more

የአምቡላንሱ ችግር የሰርክ ችግር እንዳይሆን

የአምቡላንሱ ችግር የሰርክ ችግር እንዳይሆን

የአምቡላንሱ ችግር የሰርክ ችግር እንዳይሆን

የአምቡላንሱ ችግር የሰርክ ችግር እንዳይሆን

ጥር ፲፬ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም. የተፈጸመው ሕገ ወጥ ሢመተ ጳጳሳት በነገ የቤተ ክርስቲያን ታሪክ እና በዛሬው አገልግሎቷ ጥቁር አሻራ የተወ ክሥተት ሆኖ እየታወሰ ይኖራል፡፡ ሕገ ወጥ ሹመቱ የፈጠረውን ችግር ለማረም ቅዱስ ሲኖዶስ የሔደበትን መንገድ በቀኖና ቤተ ክርስቲያን እና በሕገ ቤተ ክርስቲያን ሚዛን መዝነው የሚተቹ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን እና ሌሎች የቤተ ክርስቲያን ልጆች በርካታ ናቸው፡፡ የሲኖዶስ አባላት የሆኑ ሊቃነ ጳጳሳት ደግሞ የችግሩን ምንጭ ያደርቃል ብለው ያሰቡትን ወስነዋል፡፡ በውጤቱም የተከሠተውን ችግር ለመፍታት በዋናነት ኦሮሚያ ክልል ለሚገኙ ሀገረ ስብከቶች በአፋን ኦሮሞ ማስተማር የሚችሉ ኤጲስ ቆጶሳትን መርጠው ሾመዋል፡፡ ቅዱስ ሲኖዶስ የወሰደውን የመፍትሔ አቅጣጫ ለሕዝበ ክርስቲያኑ ለማስረዳት ብፁዐን አበው በቤተ ክርስቲያኗ መገናኛ ብዙኃን ቀርበው መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ በመግለጫው ላይ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ ሲኖዶሱ የቆየበትን ፈታኝ ቅርቃር እንደሚከተለው በፈሊጥ ነበር የገለጹት፡፡ Read more

“የመንበረ ሰላማ” እና “የትግራይ ጠቅላይ ቤተ ክህነት” ጉዳይ

“የመንበረ ሰላማ” እና “የትግራይ ጠቅላይ ቤተ ክህነት” ጉዳይ

 “የመንበረ ሰላማ” እና “የትግራይ ጠቅላይ ቤተ ክህነት” ጉዳይ

“የመንበረ ሰላማ” እና “የትግራይ ጠቅላይ ቤተ ክህነት” ጉዳይ

በትግራይ ክልል የሚገኙ አህጉረ ስብከት ሊቃነ ጳጳሳት በሰሜኑ የአገራችን ክፍል በተከሠተው  ጦርነት ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን የአስተዳደር ክፍተት በማስተካከል ግንኙነቱ እንዲቀጥል በብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርኩ ለተጻፉ ደብዳቤዎችም ሆነ በአካል በመሔድ ያቀረቡትን የሰላም ጥያቄ በመግፋት ክልላዊ ሲኖዶስ ለማቋቋም የሚያደርጉትን ሒደት አጠናክረው ቀጥለዋል። መንበረ ሰላማ የሚባል መንበር፣ የትግራይ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሊቃነ ጳጳሳት ጉባኤ ጽ/ቤት የተሰኘ መዋቅር እንደፈጠሩ በደብዳቤዎቻቸውና በመግለጫዎቻቸው አሳውቀዋል። ከዚህም አልፈው ሐምሌ ፱ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ለአገር ውስጥ አምስት ለውጪ አምስት አህጉረ ስብከት በአጠቃላይ አሥር “ኤጲስ ቆጶሳትን” እንደመረጡ አሳውቀዋል። ጳጳሳቱ በዚህ ሳይገቱ ሐምሌ ፲፮ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም መረጥናቸው ካሏቸው ውስጥ ስድስቱን ሾመዋል። የተፈጸመው ድርጊት ከቀኖና ቤተ ክርስቲያን ውጭ የሆነ፣ የቤተ ክርስቲያንን አንድነት የሚፈታተን፣ ሐዋርያዊነቷን የሚያቃልል፣ ቅድስትነቷን የማይቀበል፣ ኵላዊነቷን በጎጥ የከፋፈለ ድርጊት በመሆኑ የማያዳግም መፍትሔ ሊሰጠው ይገባል። በዚህ ጽሑፍ በመጠኑ መዳሰስ የምንፈልገው የትግራይ ቤተ ክህነትን የትመጣ፣ ለጉዳዩ እንደ ገና መቀስቀስ ገፊ ምክንያቶች፣ የእንቅስቃሴው መሪዎችና ግባቸውን በተመለከተ ነው። Read more