የሰላም ዋጋው ስንት ነው?

የሰላም ዋጋው ስንት ነው?

የሰላም ዋጋው ስንት ነው?

የሰላም ዋጋው ስንት ነው?

ሰላም የሚለው ቃል ሲጠራ ቀላል ቢመስልም ዋጋው ግን በገንዘብ ከመተመን በላይ ነው፡፡ ሰላም እንኳን ለሰው ልጅ ለእንስሳት፣ ለአራዊት እና በጠቅላላው ለሥነ ፍጥረት በጣም አስፈላጊ ነገር ነው፡፡ ሰላም ከሌለ ማንም ወጥቶ መግባት፣ ነግዶ ማትረፍ፣ አርሶ መብላት፣ ደግሶ መዳር አይችልም፡፡ ሠርቶ የመለወጥን ተስፋም ያመነምናል፡፡ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በጸሎተ ቅዳሴዋ “እግዚአብሔር በይቅርታው አንድ ያደርገን ዘንድ ስለ ሰላም እንማልዳለን፤ በዘመኑ ሁሉ ፍጹም ሰላምን እግዚአብሔር ይሰጣት ዘንድ እግዚአብሔርን ስለምትወድ ስለ አገራችን ኢትዮጵያ እንማልዳለን” በማለት ዕለት ዕለት ፈጣሪዋን የምታሳስበው ያለ ምክንያት አይደለም – ሰላም የሁሉ ነገር መሠረት ስለሆነ እንጂ፡፡ እንኳን ሰማያዊ ለሆነው ሃይማኖት ለምድራዊ ኑሮም ቢሆን ዓለም የምትሸልመው ሳይታክቱ ለሰላም የደከሙትን ነው፡፡ Read more

ባይተዋርነት እስከ መቼ?

ባይተዋርነት እስከ መቼ?

ባይተዋርነት እስከ መቼ?

ባይተዋርነት እስከ መቼ?

 መስከረም ፲፭ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም. በአርሲ ሀገረ ስብከት በሆንቆሎ ዋቤ ወረዳ ቤተ ክህነት ኦርቶዶክሳውያን ተገደሉ (ሰባት ኦርቶዶክሳውያን)፡፡ ኦርቶዶክሳውያን ጨቅላ ሕፃናትን ጨምሮ የካህናት ቤተሰብ በአሰቃቂ ሁኔታ በጥይት ተደብድበው ተገደሉ፡፡ በርካቶች ቆሰሉ፡፡
 ካህናት እና ቤተሰቦቻቸው ከቤተ ክርስቲያን እስከ ቤታቸው ታድነው ይገደላሉ፡፡
 መስከረም ፳፫ ቀን ፳፻፲፮ ዓ.ም.) በምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት በአዳማ ዙሪያ ወረዳ ቤተ ክህነት በአርቱ መካነ ቅዱሳን ቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን አገልጋዮች የሆኑት አባ ተክለ አብ እና ቀሲስ መሠረት ተገደሉ፡፡ በደራ፣ በወለጋ፣ በቤንሻንጉል ወዘተ
 አሮጌው ዓመት(፳፻፲፭ ዓ.ም.) በስልጤ ዞን የተለመደውን የኦርቶዶክሳውያን ደም በማፍሰስ፣ ሀብት ንብረታቸውን በማቃጠል እና በማሳደድ ነው የተሰናበተን፡፡ አዲሱ ዓመት ደግሞ የአሮጌውን ዓመት የደም ግብር መገበርን አጠናክሮ ቀጥሎበታል፡፡
 ካህኑ በዐውደ ምሕረት በአገልግሎት ላይ እያሉ በጥይት የተመቱት ጠረፍ አካባቢ በምትገኘው አጥቢያ አይደለም፡፡ እዚሁ አዲስ አበባ ነው፡፡ Read more

ክርስትና ከዘውግ ባሻገር የሆነ ማንነት

ክርስትና ከዘውግ ባሻገር የሆነ ማንነት

ክርስትና ከዘውግ ባሻገር የሆነ ማንነት

ክርስትና ከዘውግ ባሻገር የሆነ ማንነት

የሰው ልጅ ሁሉ ከአዳም የተገኘ የእግዚአብሔር አምላክ የእጅ ሥራ ነውና ከላይ በቀለም በቅርፅ ወዘተ ልዩነት ቢኖረው እንኳ የሚመሳሰልበት ከውስጥ የሆነ ሥነ-ሕይወታዊ አንድነት አለው፡፡ ይህም ተመሳሳይ ተፈጥሮአዊ እና ሥነ ልቡናዊ (Bio-Psychic Union) ውቁር እንዲኖረው አድርጓል፡፡ በማኅበራዊ ፍጡርነቱ በፈጠረው በማኅበራዊ መስተጋብሩ ምክንያት ደግሞ በሒደት ራሱን ካንድ የባህል መሠረት ካለው ማንነት ጋር ያዛምዳል፡፡ ይህ ልዩነት ደግሞ የተለያየ አስተሳሰብ/ እና የአረዳድ አድማስ እንዲኖረው ያደርገዋል፡፡ ክርስትና ለነፍሳችን መድኅን የሆነው የእውነትና የሕይወት መንገድ ጌታችን መድኃኒታችን ክርስቶስ ኢየሱስ ብቻ መሆኑን ያስተምራል፡፡ ክርስቲያንም ይህን እውነት ብቻ ይከተላል፡፡ ከአምልኮ መልስ ባለው ማኅበራዊ መስተጋብር ግን ብዝኃነትን ያከብራል፡፡ Read more

ነፋስን ዘርተዋል፤ ዐውሎ ነፋስንም ያጭዳሉ (ሆሴ. ፰፡፯)

ነፋስን ዘርተዋል፤ ዐውሎ ነፋስንም ያጭዳሉ (ሆሴ. ፰፡፯)

ነፋስን ዘርተዋል፤ ዐውሎ ነፋስንም ያጭዳሉ (ሆሴ. ፰፡፯)

ነፋስን ዘርተዋል፤ ዐውሎ ነፋስንም ያጭዳሉ (ሆሴ. ፰፡፯)

ቸርነት የባሕርይ ገንዘቡ የሆነው አምላካችን እግዚአብሔር “ብትወዱኝስ ትእዛዜን ጠብቁ” ብሏል። ትእዛዛቱን በመጠበቅ የሚገኘው ክብር ደግሞ የዘለዓለም ሕይወት መሆኑን ገልጾልናል። የምንጠብቃቸውን ትእዛዛት በተመለከተ ደግሞ አንድ ሕግ ዐዋቂ “ከሕግ ማናቸይቱ ትእዛዝ ትልቅ ናት?” ብሎ በጠየቀው ጊዜ ጌታ የሰጠው መልስ “አምላክህን በፍጹም ልብህ፣ በፍጹም ነፍስህ፣ በፍጹም አሳብህ ውደድ። ታላቂቱ እና ፊተኛይቱ ትእዛዝ ይህች ናት። ሁለተኛይቱም ይህችን ትመስላለች። እርስዋም ባልንጀራህን እንደ ነፍስህ ውደድ የምትለው ናት። በእነዚህ በሁለቱ ትእዛዛት ሕግም ሁሉ ነቢያትም ተሰቅለዋል” (ማቱ. ፳፪፡፴-፮፵) የሚል ነው። ከእነዚህ ከሁለቱ ትእዛዛት የሚወጣ ሕግ እና ትእዛዝ የለም። ሁሉም ሕግጋት ፍቅረ እግዚአብሔርን እና ፍቅረ ቢጽን መሠረት ያደረጉ ናቸው። እነዚህን ትእዛዛት ማክበር በምድር ላይ ሰላምን ይሰጣል፤ ዕድሜን ያረዝማል፤ በሰማይ የዘለዓለም ሕይወትን ያስገኛል። Read more