እርሱን የምሾመው ለመንበሩ ክብር እንዲሰጠው ነው

እርሱን የምሾመው ለመንበሩ ክብር እንዲሰጠው ነው

እርሱን የምሾመው ለመንበሩ ክብር እንዲሰጠው ነው

እርሱን የምሾመው ለመንበሩ ክብር እንዲሰጠው ነው

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “አሁንም በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። ከእኔ በኋላ ለመንጋዪቱ የማይራሩ ነጣቂዎች ተኵላዎች እንደሚመጡ እኔ አውቃለሁ። ደቀ መዛሙርትንም ወደ እነርሱ ይመልሱ ዘንድ ጠማማ ትምህርትን የሚያስተምሩ ሰዎች ከእናንተ መካከል ይነሣሉ። ስለዚህም ትጉ፤ እኔ ሁላችሁንም ሳስተምር ሦስት ዓመት ሙሉ ሌትም፣ ቀንም እንባዬ እንዳልተገታ አስቡ። አሁንም ለእግዚአብሔርና ሊያነጻችሁ በቅዱሳንም ሁሉ መካከል ርስትን ሊሰጣችሁ ለሚችለው ለጸጋው ቃል አደራ ሰጥቻችኋለሁ” (ሐዋ. ፳÷ ፳፰-፴፪)¹ በማለት ያስተማረው ትምህርት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ኤጲስ ቆጶሳትን ስትመርጥ በጣም እንድትጠነቀቅ የሚያሳስብ ቃል ነው። Read more

ኤጲስ ቆጶስ ለመሾም የሚያገለግለው መስፈርት

ኤጲስ ቆጶስ ለመሾም የሚያገለግለው መስፈርት

ኤጲስ ቆጶስ ለመሾም የሚያገለግለው መስፈርት

ኤጲስ ቆጶስ ለመሾም የሚያገለግለው መስፈርት

ኤጲስ ቆጶሳት የአህጉረ ስብከታቸውን ክርስቲያኖች በአባትነት የሚጠብቁ፣ በመምከር ችግራቸውን የሚያቃልሉ፣ በማንኛውም ነገር አርአያ የሚሆኑ ናቸው። በዓመት ሁለት ጊዜ በሚደረገው የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባኤ በመሳተፍ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሚጠቅሙ ውሳኔዎች እንዲተላለፉም የድርሻውን ይወጣሉ። ይህም የአገልግሎቱን ከባድነት ሲያመለክት ለከባድ አገልግሎት የሚታጨው አባትም ኃላፊነቱን በመደንብ መወጣት የሚችል መሆኑን ይገባዋል። Read more

‹‹በበጎነት ላይ ዕውቀትን ጨምሩ›› (፪ኛ ጴጥ. ፩፥፭-፯)

‹‹በበጎነት ላይ ዕውቀትን ጨምሩ›› ፪ኛ ጴጥ. ፩፥፭-፯

‹‹በበጎነት ላይ ዕውቀትን ጨምሩ››(፪ኛ ጴጥ. ፩፥፭-፯)

‹‹በበጎነት ላይ ዕውቀትን ጨምሩ››
(፪ኛ ጴጥ. ፩፥፭-፯)

ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ መሆኑን አምነው ከተከተሉት መካከል ጥቂቶችን መረጦ ሐዋርያትን ሾመ፡፡ እስከ ዛሬ ድረስ በእረኛውና በመንጋው መካከል ላለው መስተጋብር መሠረት አስቀመጠ፡፡ የዛሬዎቹ አበው ጳጳሳት እና ካህናት የዚህ ሐዋርያዊ ውርስ ተቀባዮች ናቸው፡፡ በሐዋርያነት የተሾሙት ለተጠሩበት ሐዋርያዊ አገልግሎት ስኬት የሚያስፈልጋቸውን ሥነ ምግባርና ዕውቀት ከጌታ በነቢብም በገቢርም ተምረዋል፡፡ ዛሬም ድረስ ለተጠሩበት አገልግሎት የሚመጥን ሥነ ምግባር እና ትምህርት (ዕውቀት) የሢመተ ጵጵስና ሁለት ምሰሶዎች ናቸው፡፡ Read more

ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳትና የምእመናን ሱታፌ

ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳትና የምእመናን ሱታፌ

ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳትና የምእመናን ሱታፌ

ሢመተ ኤጲስ ቆጶሳትና የምእመናን ሱታፌ

የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ምእመናንን ማእከል ያደረገ ነው። ጌታችን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሐዋርያትን የሰጣቸው ዋናው ትእዛዝ “አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችኋቸውና ያዘዝኋችሁን ሁሉ እንዲጠብቁ እያስተማራችኋቸው ደቀ መዛሙርቴ አድርጓቸው” (ማቴ. 28፡19-20) የሚል ነው። ስለሆነም ሐዋርያትና በሐዋርያት እግር የተተኩት ሐዋርያውያን አበው፣ ዐቃብያነ እምነት፣ ሊቃውንት በአጠቃላይ በየዘመኑ የተነሡ የቤተ ክርስቲያን አባቶች ዋና ግብራቸው ይህን ታላቁን ተልእኮ መፈጸም ነበር። ጌታችን ከሙታን ተለይቶ ከተነሣ በኋላ ለሐዋርያት ለሦስተኛ ጊዜ በተገለጠላቸው ወቅት ስምዖን ጴጥሮስን ሦስት ጊዜ ትወደኛለህን? ብሎ እየጠየቀ የሰጠው ትእዛዝም በተመሳሳይ “ግልገሎቼን አሰማራ፣ ጠቦቶቼን ጠብቅ፣ በጎቼን አሰማራ” (ዮሐ. 21፡15-17) የሚል ነው። Read more

እንኳን ደስ አለዎ ወይስ እግዚአብሔር ያስችልዎ?

እንኳን ደስ አለዎ ወይስ እግዚአብሔር ያስችልዎ?

እንኳን ደስ አለዎ ወይስ እግዚአብሔር ያስችልዎ?

እንኳን ደስ አለዎ ወይስ እግዚአብሔር ያስችልዎ?

ኤጲስ ቆጶስነት ምቾትን አብዝቶ ለሚሻው፣ አድልኦንና ወገንተኝነት ለሚስማማው ለሥጋ ጠባይ የሚመች ሓላፊነት አይደለም፡፡ ሰዋዊ ባሕርይን ገርተው የነፍስ ባሕርይን ገንዘብ ወደሚያደርጉበት ማዕርግ የሚሰግሩበት ራስን በመካድ መሠረት ላይ የቆመ የእግዚአብሔር ጥሪ ነው፡፡ ክህነት ትሑት ሰብዕናን የሚሻ የአገልግሎት ሥልጣን ነው፡፡ አንዱን ከሌላው አስበልጠው ለመጥቀም፣ ያልተደሰቱበትን ደግሞ ከሌላው በታች አድርገው ለመጉዳት ለቂም መወጫነት ዐስበው የሚሹት በትረ ሥልጣን አይደለም፡፡ የቂም በትር ወይም የድሎት መወጣጫ እርካብ ላድርግህ ቢሉት ባለቤቱ እውነተኛው ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ክርስቶስ (ዕብ. ፯፥፳፰) መክሊቱን የጠየቀ ዕለት መሸሸጊያ ጥግ ይጠፋል፡፡ እናም ኤጲስ ቆጶሳት አገልግሎታቸውን የሚፈጽሙት እውነተኛ ዳኝነት የባሕርይው በሆነ በእግዚአብሔር ፊት መሆኑን ለአፍታ መዘንጋት እንደሌለባቸው ቤተ ክርስቲያን አበክራ ታስገነዝባለች፡፡

Read more

አክሊል የሆነችው ሢመት መርጣ የምታርፍባቸው አባቶች

አክሊል የሆነችው ሢመት መርጣ የምታርፍባቸው አባቶች

አክሊል የሆነችው ሢመት መርጣ የምታርፍባቸው አባቶች

አክሊል የሆነችው ሢመት መርጣ የምታርፍባቸው አባቶች

ባለፉት ሁለት ተከታታይ ጽሑፎች ቤተ ክርስቲያን ያለችበትን የአመራር ሁኔታና የሚያስፈልጋትን አመራር ተመልክተናል። በዚህ ክፍል ደግሞ የሚፈለገውን አመራር ለመስጠት የሚችለው ምን መስፈርቶችን የሚያሟላ አባት ነው የሚለውን እንመለከታለን። የኤጲስ ቆጶስነት ሢመት ለሚገባው አባት አክሊል ስትሆን ለማይገባው ደግሞ እሾህ እንደምትሆንበት ቤተ ክርስቲያን ታሪክ ሲከሠት የኖረ እውነት ነው። መንፈሳዊት ሢመት አክሊል የምትሆነው ኖላዊነታቸውን አምነው የተጣለባቸውን አደራ ለመወጣት ለሚተጉ አባቶች ሲሆን እሾህ የምትሆነው ደግሞ ሳይገባቸው ሰማያዊውን ምሥጢር ጊዜያዊ ጥቅም ለማግኘት ለሚሞክሩ ሲሞናውያን ነው። ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ኤጲስ ቆጶሳትን የምትሾመው ምእመናንን ከአውሬ እንዲጠብቁ ለኖላዊነት ነው። ኖላዊደግሞ በበር የሚገባ ጠባቂ፣ ነፍሱን ስለበጎቹ አሳልፎ የሚሰጥ ዋስ፣ “ደጃፍ የመለሰውን፣ ማጀት የጎረሰውን” ለልጆቹ እንደሚያወርስ አባት ነው። መንፈሳዊ አባት ተብሎ የሽፍታ ተግባር የሚፈጽም፣ ኖላዊነቱን ዘንግቶ ምንደኛ የሚሆን፣ ሰማያዊውን ሢመት በጊዜያዊ ጥምቅ የሚለውጥ፣ አምላካዊውን አደራ ዘንግቶ ፈቃደ መንግሥትን ለመፈጸም የሚደክም ከሆነ ሢመት አክሊል መሆኗ ቀርቶ እሾህ ትሆናበታለች። Read more

ቤተ ክርስቲያን ምን ዓይነት አመራር ያስፈልጋታል?

ቤተ ክርስቲያን ምን ዓይነት አመራር ያስፈልጋታል?

 

ቤተ ክርስቲያን ትውልዱን ለእግዚአብሔር መንግሥት የማዘጋጀት ሰማያዊ ተልእኮዋን በአግባቡ ለመወጣት እና የነገውን ትውልድ ሰብእና በመቅረፅ ረገድ የሰብአዊ ምሕንድስና ሥራዋን ለመፈጸም ዘመኑን የዋጀ አመራርና አሠራር ያስፈልጋታል። ይህም መሻት በብዙ ኦርቶዶክሳውያን ልብ ውስጥ አለ፡፡ ይህ ዕውን ይኾን ዘንድ ዛሬም ኾነ ነገ ቤተ ክርስቲያን ስንዱ እመቤት የሚያሰኛትን የነገረ ሃይማኖት ጥንቃቄ በአስተዳደርና በአመራርም መድገም ስትችል ነው። ቤተ ክርስቲያን በምድር ያለች የእግዚአብሔር መንግሥት ናትና መሠረታዊ መገለጫዎቿ ተጠብቀው ብቻ በምትሰጣቸው የአመራርነት ሚናዋ ተገልጠው ሊታዩ ይገባል። ይህን ዕውን ማድረግም በየዘመኑ የሚነሡ ኖላውያን እና ምእመናን የሁል ጊዜ ሓላፊነት ነው፡፡

በተለይም ቤተ ክርስቲያን ከውጭና ከውስጥ ተገዳዳሪዎች ጋር በተፋጠጠችበት እና እንደ ኢዮብ በፈተና በተከበበችበት በዚህ ዘመን የአሳዳጆቿን በትር መቋቋም የምትችለው በምትሰጠው ውጤታማ አመራር ነው። ፈተናውን ከባድ የሚያደርገው ከውጪው ተጽእኖ በላይ በውስጥ ያለው መንፈሳዊነት መዳከም እና ብልሹ የአስተዳደር ሥርዐት መስፈን ነው፡፡ ስለዚህ ቤተ ክርስቲያን በጥንቱ መንፈሳዊ ልዕልናዋ ጸንታ እንድትቆም ማስቻል እና በዘመኑ የአስተዳደር ጥበብ የተዋጀ አሠራር የሰፈነባት መንፈሳዊ ተቋም ማድረግ በሁለቱ ተገዳዳሪዎቿ የተሴረባትን ሴራዎች ማምከኛ መንትያ መንገዶች ናቸው፡፡

Read more

“የእግዚአብሔር መልአክ በሚፈሩት ሰዎች ዙሪያ ይሰፍራል ያድናቸውማል።” መዝ 33:7

👉 ይህን ኃይለ ቃል የተናገረው ልበ አምላክ ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ነው። በግልጽ እንደነገረን የእግዚአብሔር የሆኑት ቅዱሳን መላእክት የሚያድኑ አዳኞች ናቸው። እነርሱን ከሚፈሯቸውና ከሚያምኗቸው ሰዎች አይለዩም። ከሚደርስባቸው መከራ እና ችግር ፈተና ሁሉ ያድኗቸዋል ይታደጓቸዋል። ቅዱሳን መላእክት የሰው ልጆችን የሚያድኑ አዳኞች መሆናቸውን ቅዱስ ያዕቆብ ዮሴፍንና ልጆቹን በባረከ ጊዜም እንዲህ ሲል መስክሯል። “ከታናሽነቴ ጀምሮ እኔን የመገበኝ እግዚአብሔር ከክፉ ነገር ሁሉ #ያዳነኝ_መልአክ እነዚህን ብላቴኖች ይባርክ።” ዘፍ 48:15

Read more

፲፪ኛው የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ የአቋም መግለጫ

በኢ/ኦ/ተ/ቤ የሰ/ት/ቤቶች ማ/መምሪያ የዓለም አቀፍ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ፲፪ኛው ዓመታዊ ጠቅላላ ጉባኤ ከግንቦት 26-27 ቀን 2015 ዓ.ም ተከናውኖ
በቀረቡ ሪፖርቶች፣ ጥናታዊ ሰነዶች፣ ከሁሉም አካባቢዎች ከቀረቡ የውይይት ግብዓቶች በመነሳት ባለ አስራ አንድ ነጥብ የአቋም መግለጫ በማውጣት ተጠናቋል።

1.  በ12ኛው ጠቅላላ ጉባኤ የቀረበውን ሪፖርትና ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫ ተቀብለን አጽድቀናል ለትግበራው በጋራ እንሰራለን፡፡
2.  ከጠቅላይ ቤተክህነት ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃና መምሪያ ሀገር አቀፍ ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት እስከ አጥቢያ ሰ/ት/ቤት የቀረበውን የአደረጃጀት መዋቅር በጥልቀት ገምግመናል፡፡በጉባኤው የተሰጡ ማስተካከያዎችን በማካተት ወደ ስራ እንዲገባ ወስነናል፡፡
3.  የሥርዓተ ትምህርት መጻሕፍትን ለማሳተም የበጀት እጥረት እንዳለ ተገንዝበናል፡፡ይህንን ከቅዱስ ሲኖዶስ እስከ ሀገረ ስብከት ያሉ የቤተክርስቲያን መሪዎች በመገንዘብ ለሕትመቱ ተዘዋዋሪ በጀት/Revolving budget/ እንዲፈቀድና የተዘጋጁ መጻሕፍት ወደ ሕትመት እንዲገቡ በየደረጃው ለሚመለከታቸው አካላት ጥያቄ እንዲቀርብና ክትትል እንዲደረግ በአጽንዖት እንጠይቃለን፡፡
4.  ሀገሪቱ ላይ በሚከሰቱ የተለያዩ አለመግባባቶች ምክንያት ያለ እዳዋ እዳ የተሸከመችው ቅድስት ቤተክርስቲያናችንን በአቢያተ ክርስቲያኗ ላይ የሚደርሰው መቃጠልና መዘረፍ በምእመናን እንዲሁም በሰንበት ት/ቤት ወጣቶቻችን ላይ የሚደርስ የህይወት መጥፋት፣ የአካል መጉደልና መሳደድ እንዲቆም የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ እንጠይቃለን፡፡
5.  በተለያ ምክንያት የቤተ ክርስቲያንን መምህራንና አገልጋዮችን ማሰር እንዲቆም የሚመለከታቸው አካላት በሙሉ የበኩላቸውን ድርሻ እንዲወጡ እንጠይቃለን፡፡
6.  የቤተክርስቲያናችን አንድነት ተጠብቆ ምዕመናን ከመደናገር ወጥተው ሥርዓተ አምልኮ በነጻነት መፈጸም ይችሉ ዘንድ ይቅርታና ሰላምን ሲያስተምሩ የኖሩ የትግራይ አህጉረ ስብከት ሊቃነ ጳጳሳትና የአስተዳደር አካላት ለቤተክርስቲያ አንድነትና ለምዕመናን ሲሉ ወደ ውይይትና ይቅርታ እንዲመለሱና ቅዱስ ሲኖዶስ ያቀረበውን የሰላም ጥሪ እንዲቀበሉ በልጅነት መንፈስ እየጠየቅን ቅዱስ ሲኖዶስና በአንጻራዊ ሰላም ውስጥ ያለው የቤተ ክርስቲያን መዋቅር በትግራይ በተፈጠረው ጦርነት ለተፈጠረው ችግር ተገቢውን ድጋፍ ትኩረት ሰጥቶ እንዲሰራ እንጠይቃለን፡፡
7.  በቃለ አዋዲ የተደነገገው የሰበካ አስተዳደር ጉባኤ አደረጃጀት ከአጥቢያ ቤተክርስቲያን በቀር እየተተገበረ አለመሆኑ በቤተክርስቲያን አስተዳደራዊ ሂደት ላይ ክፍተት እንደፈጠረ በጉባኤው በጥልቀት ተነስቷል፡፡ስለሆነም ከወረዳ ቤተክህነት እስከ ጠቅላይ ቤተክህነት ድረስ በቃለ አዋዲው መሰረት የካህናት፣የምዕመናን እና የሰንበት ት/ቤት አባላት ተሳትፎ እንዲከበር በታላቅ አጽንዖት እንጠይቃለን፡፡
8.  ሥርዓተ አምልኮ ለመፈጸም፣ልጆች ወልዶ ለማሳደግና ተተኪ ትውልድ ለማፍራት ሀገር ያስፈልጋል፡፡በሀገር ውስጥም ሰላም ከሌለ ምንም ማከናወን አይቻልምና በመላው ሀገሪቱ በተቃርኖ የሚገኙ አካላት በሚያርጉት ጦርነትና የእርስ በእርስ ግጭት ምክንያት ንጹሀን ዜጎች ሕጻናት፣ሴቶችና ካህናት ላይ የሚደርስ እንግልትና ጉዳት እየከፋ መምጣቱን በመገንዘብ ልዩነታቸውን በውይይትና በድርድር ብቻ እንዲፈቱ እንጠይቃለን፡፡
9.  ከሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት ጋር ተያይዞ የሚፈጠሩ ችግሮች በፍጹም ቅድስት ቤተክርስቲያናችንን የሚመጥኑ ሆነው አላገኘናቸውም፡፡በመሆኑም ሲመቱ ሕገ ቤተክርስቲያንን፣ፍትሐነገሥትንና ቃለ አዋዲን ባከበረና ባከበረ መልኩ ብቻ እንዲደረግ በልጅነት መንፈስ እንጠይቃለን፡፡
10.  በቤተክርስቲያናችን የሚስተዋሉ ችግሮችን በዘላቂነት ለመፍታት በተለያዩ የቤተ ክርስቲያን አካላት ተጠንተው የሚቀርቡ የመፍትሔ ሀሳቦችን ቅዱስ ሲኖዶስ በምክረ ሃሳብነት እንዲቀበላቸውና በማዳበር እንዲተገበሩ አቅጣጫ እንዲሰጥ ከጠቅላይ ቤተክህነት ጀምሮ ያሉ የቤተ ክርስቲያን መዋቅር አካላት የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ ያለምንም መሸራረፍ ተግባራዊ እንዲያደርግ በአጽንዖት እናሳስባለን፡፡
11.  በቤተክርስቲያናችን ውስጥ የሚስተዋሉ የአስተዳደር ችግሮች እንዲፈቱ በሚያስችሉ ሥራዎች ላይ ሁሉ በመሳተፍና እንደ ቤተክርስቲያን ተተኪ ልጅነታችን የበኩላችንን ኃላፊነት በባለቤትነት መንፈስ ከጠቅላይ ቤተ ክህነት እስከ አጥቢያ ባለዉ መዋቅር ትኩረት ሰጥተን የምንሠራ መሆኑን እንገልጻለን፡፡

ግንቦት 27 ቀን 2015 ዓ.ም
አዲስ አበባ
ኢትዮጵያ

ዕርገተ ክርስቶስ

“እያዩት ከፍ ከፍ አለ፤ ደመናም ከዓይናቸው ሰውራ ተቀበለችው” ሐዋ. 1÷9

ዕርገት ማለት ወደላይ ከፍ ከፍ ማለት ሲሆን የመሬትን የስበት ኃይል የሚያሸንፍ ከፍታ ነው፡፡ ክርስቶስ ወደ ሰማይ ያረገው የመሬት የስበት ኃይልሳይገድበው ነው፡፡ የክርስቶስ ዕርገት ቀድሞ በትንቢት የተነገረ፤ በሚያምኑት ዘንድ በናፍቆት ሲጠበቅ የቆየ እና በራሱ በጌታችን የተሰበከ ነው፡፡

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለ፴፫ ዓመታት ከሦስት ወራት በምድር ኖሯል፡፡ በ፴ ዓመቱ ተጠመቀ ለ፫ ዓመታት አስተማረ፣ ስለ ኃጢአታችን በመስቀል ላይ ቤዛ ሆነልን፡፡ በሦስተኛውም ቀን ከሙታንተለይቶ ተነሣ፤ ለደቀ መዛሙርቱም ተገለጠላቸው፡፡ Read more