የኤጲስ ቆጶሳት አስመራጭ ኮሚቴ ያከናወናቸው ተግባራትና ትኩረት ሊደረግባቸው የሚገባቸው ጉዳዮች

የኤጲስ ቆጶሳት አስመራጭ ኮሚቴ ያከናወናቸው ተግባራትና ትኩረት ሊደረግባቸው የሚገባቸው ጉዳዮች
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በግንቦት ፳፻፲፭ ዓ.ም በነበረው የርክበ ካህናት መደበኛ ጉባኤው ዘጠኝ አዲስ ኤጲስ ቆጶሳትን ለመሾም ሰባት ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ያሉበት አስመራጭ ኮሚቴ መሠየሙ ይታወቃል። አዲስ ኤጲስ ቆጶሳት የሚመደብባቸው ዘጠኙ አህጉረ ስብከትም ምዕራብ ወለጋ፣ ምሥራቅ ወለጋ፣ ሆሮ ጉዱሩ ወለጋ፣ ምዕራብ አርሲ (ሻሸመኔ)፣ ድሬ ዳዋ፣ ምሥራቅ ሐረርጌ፣ ቡኖ በደሌ፣ ጌዴኦ፣ ቡርጂና አማሮ እንዲሁም ዳውሮ ኮንታ አህጉረ ስብከት ናቸው። የአስመራጭ ኮሚቴው አባላት ደግሞ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ፣ ብፁዕ አቡነ ማርቆስ፣ ብፁዕ አቡነ ሳዊሮስ፣ ብፁዕ አቡነ ኤርምያስ፣ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል፣ ብፁዕ አቡነ ሕርያቆስና ብፁዕ አቡነ ሩፋኤል ሲሆኑ አስመራጭ ኮሚቴው ግንቦት ፳፫ ቀን ፳፻፲፭ ዓ.ም ሥራውን በይፋ የጀመረ መሆኑን የጠቅላይ ቤተ ክህነት ሕዝብ ግንኙነት አገልግሎት አሳውቋል። Read more