የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት - በኢ/ኦ/ተ/ቤ የመንበረ ፓትርያርክ ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ አንድነቱ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ተቋማዊ ራእይ፣ ተልእኮ
      • መዋቅራዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቋማዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማስፈጸሚያ
    • ስልታዊ እቅድ 2018 – 2021 ዓ/ም
  • ሥርዓተ ትምህርት
    • መሠረታዊ መረጃዎች
    • የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት አደረጃጀት መመሪያ
    • የሥርዓተ ትምህርቱ መመማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
    • የሥርዓተ ትምህርቱ ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ /ካሌንደር
    • የመምህራን ሥልጠና እና መልእክቶች
    • መጻሕፍቱን ለማግኘት እና ተጨማሪ መረጃ
    • ልዩ ልዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች
  • ፕሮጀክቶች
  • መዝሙረ ማኅሌት
    • የመስከረም ወር መዝሙሮች
      • የዮሐንስ መዝሙር
      • የመስቀል መዝሙሮች
      • የብዙኃን ማርያም መዝሙር (መስከረም ፳፩ )
      • የዘመነ ጽጌ መዝሙር
    • የጥቅምት ወር መዝሙሮች
      • የአብርሃ ወአጽብሐ መዝሙር (ጥቅምት 4 ቀን)
    • የኅዳር ወር መዝሙሮች
      • የቅዱስ ሚካኤል መዝሙር (ኅዳር 12 ቀን)
    • የጥር ወር መዝሙሮች
      • የዘመነ ጥምቀት መዝሙር
      • የቃና ዘገሊላ መዝሙር (ጥር 12 ቀን)
    • የመጋቢት ወር መዝሙሮች
      • የወርኃ ጾም መዝሙሮች
      • የሆሣዕና መዝሙራት
      • የሰሙነ ሕማማት መዝሙሮች
  • ዜና
    • አጫጭር ዜናዎች
    • ዝርዝር ዜናዎች
    • ወቅታዊ መረጃዎች
    • ማስታወቂያ
      • የሰንበት ትምህርት ቤቶች መጻሕፍት እንግሊዝኛ ትርጉም ሥራ ተሳትፎ ጥሪ
  • ያግኙን
  • ቋንቋ
    • ትግርኛ
    • Afaanoromo
  • Menu Menu

ለቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊው ለውጥ መቼ?

ለቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊው ለውጥ መቼ?

ለቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊው ለውጥ መቼ?

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ያልተበረዘ ክርስቶሳዊ ትምህርት ምንጭ ናት፡፡ ነቅ አልባ አስተምህሮዋ መቼም ቢሆን ለድርድር አይቀርብም፡፡ ከጥንትም መሥሯቿ ኢየሱስ ክርስቶስ ነውና ፍጽምት አድርጎ ነው የሠራት። መንገድ እና ሕይወት እኔ ነኝ ያለው ጌታ የመሠረታት ሕይወት የሚገኝባት መንገድ ናት ተዋሕዶ፡፡ ሐቁ ከእርሷ የተሻለ መንገድ የለም ሳይሆን ከእርሷ ሌላ የሕይወት መንገድ የለም ነው። አስተዳደራዊ ሥርዐትን በተመለከተ ግን ነገሮች የሚከወኑበት ሁልጊዜም ከዘመን ዘመን የተሻሻለ መንገድ ይመጣል።

ሐዋርያት መጀመሪያ የክርስቲያኖች ቁጥር አነስተኛ በነበረበት ሰዓት የዘረጉትን የአስተዳደር ሥርዓት የአማኙ ቁጥር እየጨመረ ሲመጣ ቀይረውታል። ‹‹ማዕድን እናገለግል ዘንድ የሚገባ ነገር አይደለም፤›› ብለው ሁኔታውን ያገናዘበ አስተዳደራዊ ለውጥ አደረጉ። ውሳኔው የምእመናንን ሱታፌ በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ከፍ ያደረገ፣ አዳዲስ የወንጌል መልእክተኞችን ወደ አገልግሎቱ የሳበ የለውጥ ውሳኔ ነበር፡፡ የክርስትናን ፋና ወጊ ሰማዕት ቅዱስ እስጢፋኖስን ያስገኘ እና አገልግሎቱን ያሰፋ አስተዳደራዊ ለውጥ ነበር፡፡

የዛሬዋ ቤተ ክርስቲያንም ገፊ ምክንያቶችን በመመዘን አይቀሬውን አስተዳደራዊ ለውጥ መቼ ማድረግ እንደሚገባት ልትማርበት የምትችል የታሪክ ዐውድ ነው፡፡ ቀደም ባለው ጽሑፋችን ‹‹ለቤተ ክርስቲያን ለምን ለውጥ ያስፈልጋታል?›› በሚል ርእስ ለውጥን ግድ የሚሉ ውስጣዊና ውጫዊ ግፊቶችን ተመልክተናል፡፡ በዚህ ጽሑፍ ደግሞ ይህ ለውጥ መቼ ነው መተግበር የሚኖርበት የሚለውን ሐሳብ በመጠኑ ለመዳሰስ እንሞክራለን፡፡

ቅዱስ ጳውሎስ ለመዳን ቀጠሮ መስጠት እንደማይገባ ሲያስረዳ ‹‹የተወደደው ሰዓት አሁን ነው፤›› (፪ቆሮ. ፮፥፪)ይላል፡፡ ለወንጌል አገልግሎት፣ ለቤተ ክርስቲያን ሰማያዊ ተልእኮ የሚበጅ ሥምሪት ለማድረግ ዕለተ ኅሪት ዛሬ ናት፣ ከዛሬም አሁን፤ ከዚህ የተሻለ የተመረጠ ጊዜ የለም፡፡ ቀን ሳለ ነው ልንሠራ የሚገባን፡፡ የእግዚአብሔር የሆነ ሁሉ በጎ ነው፤ በጎውን ነገር ለመሥራት ደግሞ ከዛሬ ያውም ከአሁን የተሻለ ጊዜ የለም፡፡ እግዚአብሔር ለለውጥ እንድንዘጋጅ በተለያየ መንገድ እየነገረን ያለበት ይህ ጊዜ ለእኛ የተወደደ ሰዓት ነው፡፡ ‹‹ጌታም ከእነርሱ ጋር ይሠራ ነበር፤›› (ማር.፲፮፥፳) እንደ ተባለ ጌታ ከእኛ ጋር የሚሠራበት ጊዜ አሁን ነው፡፡ ነገ በእጃችን አይደለምና፡፡ በይፋ የሚታየው አስተዳደራዊ ብልሹነት እና መንፈሳዊ ጉድለት ለለውጥ የሚቀጠር ጊዜ መኖር እንደሌለበት የሚያስገነዝብ የማንቂያ ደወል ነው፡፡ የውስጥና የውጭ ግፊቶች እየከበዱ መምጣት ዕለተ ኅሪት አሁን እንደሆነ አፍ አውጥተው ይናራሉ፤ ጠቢብም ይሰማቸዋል፡፡

ርትዕት የሆነችው ቤት ርቱዐን የማይኖሩባት፣ ርትዕ ሐሳብ ያላቸው የሚሳደዱባት ከሆነች ውላ አድራለች። የተበላሸው አስተዳደር የበለጠ ለመዝቀጥ ርቱዐኑን ማሳደድ፣ ሐሳውያኑን መሰብሰብ ሥራዬ ብሎ ተያይዞታል። ይህን አሠራር ማሻሻልና መለወጥ ካልተቻለ እየተደራረበ የመጣው እንከን ከመሰናክልነት ወደማይገፋ ጋራነት ብሎም ወደ አይበገሬ የችግር ተራራነት እንዲያድግ እየፈቀድንለት ነው። እዛ ደረጃ ላይ ከደረሰ በኋላ ደግሞ ላፍርስህ ቢሉት መዶሻውም ይለግማል። ማፍረስ ቢቻል እንኳ ናዳው ይዞት ገደል የሚገባ፣ የሚያዳፍነው ነገር ብዙ ነው።

የሮም ካቶሊክ ሥር ሰድዶ በቆየው አስተዳደደራዊ ዝቅጠት እና በጳጳሳቷ ዓለማዊነት የበዛበት የተቀማጠለ አኗኗር ምክንያት በሕዝቡ ዘንድ የተጠራቀመውን ምሬት ለማየት አልፈቀደችም፡፡ የካርዲናሎቿን ብልሹ ሥነ ምግባር በማረም የለውጥ ግፊቱን በጊዜውና በአግባቡ ማስተናገድ ተሳናት፡፡ ለለውጥ ዝግጁ ባልሆነ ድንዛዜ ውስጥ በመቆየቷ ፲፮ኛው ክፍለ ዘመን ላይ ከፍተኛ ዋጋ ያስከፈላትን መነሻውን አስተዳደራዊ ጥያቄ አድርጎ ወደ አስተምህሮ ልዩነት ያመራውን ሉተራዊውን አብዮት ለማስተናገድ ተገደደች፡፡ ከካቶሊክ እና ከመሰል ታሪኮች ለመማር ጊዜው አልረፈደም፡፡ አለበለዚያ በእኛ ቤተ ክርስቲያን የሚታየው መፋዘዝ እና በውስጥ ያለውን የለውጥ ጥያቄ በጊዜው ለማስተናገድ ያለመፈለግ ቅጥያ ምን ሊሆን እንደሚችል መገመት ነብይነትን አይጠይቅም፡፡ ለዛም ነው ለበጎ ሥራ ዛሬያችንን እየተጠቀምን ነገን ያማረ ማድረግ የሚኖርብን፡፡ ዛሬን ካልሠራንበት ነገ ምን ይዞ እንዲመጣ ዐናውቅም፡፡

ቅዱስ ጳውሎስ ፊሊክስ ለተባለው ሀገረ ገዢ ስለ ክርስቶስ በነገረው ጊዜ ሀገረ ገዢው አምኖ ለመጠመቅ በፊቱ የነበረን የተወደደ ሰዓት ጥሪ ቸል አለ፣ የመዳን ቀን ዛሬ እንጂ በይደር ቀጠሮ የሚተላለፍ እንዳልሆነ ዐላወቀም። «በተመቸኝ ጊዜ አስጠራሃለሁ፤» (ሐዋ. ፳፬፥፳፭) ብሎ ቀጠሮ ያዘ። ነገር ግን ሌላ ዕድል አግኝቶ ጳውሎስን አስጠርቶ ሲጠመቅና ከመንፈስ ቅዱስ ሲወለድ፣ ለሰማያዊ ሕይወት ራሱን ዕጩ ሲያደርግ የሚተርክ ምዕራፍ አላነበብንም።

ቤተ ክህነት ግልጸኝነት ያልሰፈነበትን፣ ተጠያቂነትን ከፍርድ ቀን ጋር ብቻ ያስተሣሠረ አመለካከትን እንዳነገበ ይህን ዘመን መሻገር እንደማይችል ለማወቅና ለመታረም ጊዜው አሁን ነው፡፡ የዘመኑን ተግዳሮት ዐውቆ ከውስጥ ለመጣው የለውጥ ግፊት አዎንታዊ እና አስቸኳይ ምላሽ መስጠት አማራጭ የሌለው ምርጫ ሆኖ ቀርቧል፡፡ ቤተ ክህነት የቤተ ክርስቲያንን ህልውና ከራሱ ህልውና ጋር በጥብቅ ያስሣሠረውንና ለነገ በጎነቷ ሲባል ዘመኑን የዋጀ ለውጥ በቤተ ክርስቲያን እንዲተገበር የሚመክረውን ልጇን ወደ ዳር መግፋ ማቆም አለበት፡፡ የለውጥ ደወል እየደወሉ መንፈሳዊና አስተዳደራዊ ጉድለቶች እንዲታረሙ የሚጠይቁ ልጆቿ ጉትጎታ አሁንም ሰሚ ጆሮ አጥቷል፡፡ ከነገ ዛሬ የቤተ ክህነቱን ጆሮ ለማግኘት የሚደክሙትን ድምፅ መስማት ግድ የሚልበት ሰዓት ደግሞ ከመቼውም ጊዜ በላይ ዛሬ ቀርቧል፡፡ ቤተ ክህነቱ ይህን የተወደደን ሰዓት ባልተወደደ ተግባር ላይ ማዋል መቀጠሉ የቤተ ክርስቲያንን ዘመኑን የመዋጀት ተልእኮ ያጨናግፋል፡፡ ቤተ ክርስቲያንን በለውጥ ስም ነውጥ ለደገሰላት በጥላቻ ላበደ ባዕድ እጅ አሳልፎ ይሰጣታል። ለክብርዋ ቀንተው ለውጥን ሲሹ የነበሩት ልጆቿ ምሬት ሲበዛ የሚወስዱት የተናጥል ውሳኔ ምን እንደሚሆን አይታወቅም፡፡ ቤተ ክህነት እያሳየው ያለው ለውጥ ጠል መንገድ የማይነካ ከፍታ ላይ የተቀመጡ ለሚመስላቸው የቤተ ክርስቲያን አባቶች ሳይቀር አደገኛ እንደሚሆን መገመት ግን አይከብድም፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ በመልእክቱ ‹‹ፍርድ ከእግዚአብሔር ቤት ተነሥቶ ሚጀምርበት ጊዜ ደርሷልና፤›› ይላል፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on LinkedIn
  • Share on Telegram
  • Share by Mail
https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/change.jpg 1080 1920 Abenezer Mamushet https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/logo-2-1-300x74-1.png Abenezer Mamushet2023-07-26 22:22:102023-07-26 22:34:32ለቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊው ለውጥ መቼ?
Search Search

Recent Posts

  • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ
  • ሦስተኛ ዙር የ፲፪ ክፍል ምርቃት መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት ተከናወነ።

Archives

  • April 2026
  • September 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • May 2025
  • April 2025
  • October 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • July 2022
  • June 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
© Ethiopian Orthodox Church Global Sunday School Union | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
  • Link to Youtube
  • Link to Telegram
  • Link to TikTok
Link to: ብፁዕ አቡነ አብርሃም ከትግራይ ክልል ጋር ተያይዞ ባለው ወቅታዊ ጉዳይ የሰላምና የአንድነት መልዕክት አቀረቡ Link to: ብፁዕ አቡነ አብርሃም ከትግራይ ክልል ጋር ተያይዞ ባለው ወቅታዊ ጉዳይ የሰላምና የአንድነት መልዕክት አቀረቡ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ከትግራይ ክልል ጋር ተያይዞ... Link to: ራስን በራስ መሾም በቤተ ክርስቲያን ላይ ያስከተለው መዘዝ Link to: ራስን በራስ መሾም በቤተ ክርስቲያን ላይ ያስከተለው መዘዝ ራስን በራስ መሾም በቤተ ክርስቲያን ላይ ያስከተለው...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top