እነርሱ እያቃጠሉ እኛ ስንሠራ አንኖርም

እነርሱ እያቃጠሉ እኛ ስንሠራ አንኖርም

ዘመናችን “መታዘዝ እንደ ድካም፣ ትሕትና እንደ ውርደት፣ ራስን መግዛት ራስን እንደ መጨቈን፣ በሥርዓት ማደር እንደ ኋላ ቀርነት፣ ክህነታዊ ተዋረድን የጠበቀ አገልግሎት ዘመን እንዳለፈበት የጭቆና መሣሪያ፣ ሃይማኖተኛነት እንደ ተራ ወግ አጥባቂነት ተፈርጆ ይዘመትበታል፡፡ ነባር ሃይማኖትን መቃወምን እንደ ሃይማኖት የያዘ መስተጻርርነት አየሩን ሞልቶታል” በማለት በአማን ነጸረ የጻፈው በተግባር ተገልጦ የሚታይበት ነው። ፀረ -ኦርቶዶክሶችም ይባል አክራሪዎች በኦርቶዶክሳውያን እንደሚሸነፉ ሲረዱ እግር ላይ ወድቀው የሚለምኑት በኦርቶዶክሳውያን መልካም ዕሴት ላይ ተሸጋግረው አዘናግተው ለማጥቃት ወይም ጊዜ ለመግዛት እንጂ በሚልኩት ሽምግልናም ሆነ በሚያቀርቡት ተማጽኖ አምነውበት አይደለም።
የአክራሪዎች መርሕ ራስ ብቻ ደኅና የሚል ነው። የራሳቸው ደኅንነት ከሌላው ደኅንነት ጭምር እንደሚመነጭ አመዛዝነው መረዳት የሚችሉበት አእምሮ የተነሣቸው ናቸው። መደጋገፍ የሚባለው አብሮ የመኖር ባህል፣ መከባበር የሚሉት መልካም ዕሴት አይገባቸውም። ሁሉ ነገር የእኛ፣ ሁሉን እኛ ይዘነው ሌላው ከገጸ ምድር ይጠፋ የሚል ነው። ለቀጣይ ትውልድ ማሰብ የሚባል ነገር አያውቁም። ሌላው የለፋበትን ነጥቆ መውሰድ ወይም ማውደም ሃይማኖት ብለው የያዙት እኩይ ድርጊት ነው። እግዚአብሔር የፈጠረውን ትውልድ በማጥፋት “የፈጠርከውን አጠፋንልህ” ብለው ለባለቤቱ ሪፖርት የሚያቅርቡ ናቸው። እንዲህ ያለው መረን የለቀቀ አስተሳሰብ ክቡር የሆነውን ፍጡር ከእንስሳ ተራ የሚያስመድብ ነው። Read more

ከደቂቀ እስጢፋኖስ እስከ መንበረ ሰላማ

ከደቂቀ እስጢፋኖስ እስከ መንበረ ሰላማ

ከደቂቀ እስጢፋኖስ እስከ መንበረ ሰላማ

ከደቂቀ እስጢፋኖስ እስከ መንበረ ሰላማ

የተከበራችሁ አንባብያን የዚህን ጽሑፍ የመጀመሪያ የሆነውን እና አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከተ ተሐድሶ መናፍቃን እና ተስፈንጣሪ ፖለቲከኞች የሚያነሷቸውን የፈጠራ ድርሰቶች መነሻ ምክንያት የሚያስነብበውን ጽሑፍ ለንባብ ማብቃታችን የሚታወቅ ነው። ቀጣዩን ክፍል ደግሞ እንደሚከተለው አቅርበነዋል። መልካም ንባብ፡-

ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ

በመካከለኛው ዘመን ለቤተ ክርስቲያን መልካም ካደረጉ ነገሥታት አንዱ ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ነው። ንጉሡ አገሪቱን ለሁለት ሊከፍል ጫፍ ደርሶ የነበረውን የቤተ ተክለ ሃይማኖት እና የቤተ ኤዎስጣቴዎስ ጉዳይ መፍትሔ በመስጠት ሰላም እንዲወርድ አድርጓል። ጉዳዩ እንዲህ ነው። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርሰቲያን በሐዋርያዊ አገልግሎታቸው የሚታወቁት የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም መነኰሳት እና የአባ ኤዎስጣቴዎስ ተከታዮች ልዩነት ፈጥረው ነበር። የልዩነቱ ምክንያት ቤተ ተክለ ሃይማኖቶች መከበር የሚገባት ሰንበተ ክርስቲያን እንጂ ሰንበተ አይሁድ መከበር የለባትም ሲሉ ኤዎስጣቴዎሳውያን ደግሞ ቅዳሜም፣ እሑድም መከበር አለባቸው የሚል አቋም ያዙ። በዘመኑ የነበሩ ነገሥታት አቡነ ተክለ ሃይማኖትን ያከበርን መስሏቸው የእርሳቸውን ገዳም መነኰሳት አሳብ ደግፈው ቤተ ኤዎስጣቴዎሳውያንን መግፋት በመጀመራቸው ልዩነቱ እየሰፋ ሄደ። Read more

ከደቂቀ እስጢፋኖስ እስከ መንበረ ሰላማ

ከደቂቀ እስጢፋኖስ እስከ መንበረ ሰላማ

ከደቂቀ እስጢፋኖስ እስከ መንበረ ሰላማ

ከደቂቀ እስጢፋኖስ እስከ መንበረ ሰላማ

አባ እስጢፋኖስን እና ተከታዮቹንበተመለከተ ብዙ ይጻፋል፣ ይነገራል። የእርሱ እና የተከታዮቹ ጉዳይ ማንም እንደፈለገ ለመዘወር የተመቸ ነው። ከትግራይ ክልል የተነሡ ተስፈንጣሪ ፖለቲከኞች ባላንጣችን የሚሉትን ሸዋን ለመተቸት ይጠቅሱታል። በክልሉ ኑፋቄያቸውን ለመዝራት ፈልገው ያልተሳካላቸው ተሐድሶ መናፍቃን በዕውቀቱ አቻ የሌለው፣ በአስተምህሮው እንከን የማይገኝበት አስመስለው ያቀርቡታል። ቤተ ክርስቲያኗን በዘር ለመከፋፈል የሚደክሙ አካላት አርአያነቱን እንከተል በማለት የፈጣራ ድርሰት ጽፈው ያነቡለታል። እንደ አባ እስጢፋኖስ ያለ ምግባረ ብልሹ ራሱን ኮፍሶ ሌላውን ስለሚያናንቅ እንዲህ ያለው ምግባር የመናፍቃንመለያ መሆኑን መረዳት ከተደጋጋሚ ጥፋት ይታደጋል። Read more

የትግራይ ቤተ ክህነት እንቅስቃሴ ለተሐድሶ መናፍቃን ሰርግና ምላሽ

የትግራይ ቤተ ክህነት እንቅስቃሴ ለተሐድሶ መናፍቃን ሰርግና ምላሽ

የትግራይ ቤተ ክህነት እንቅስቃሴ ለተሐድሶ መናፍቃን ሰርግና ምላሽ

የትግራይ ቤተ ክህነት እንቅስቃሴ ለተሐድሶ መናፍቃን ሰርግና ምላሽ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለሀገር ካበረክተችው አስተዋጽኦ አንዱ የሀገር አንድነት ምክንያት ሆና መኖሯ ነው። ለዚህም ነው ኢትዮጵያን ማዳከም የሚፈልጉ ኃይሎች ሁሉ መጀመሪያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ማዳከምን ዋና አጀንዳቸው የሚያደርጉት። በተለይም ከ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ ወደ ኢትዮጵያ የመጡት ሚስዮናውያን ቤተ ክርስቲያንን በማጥፋት ኢትዮጵያን መረከብ አጀንዳቸው ካደረጉ ከአራት መቶ በላይ ዘመናትን አስቈጥረዋል። በዘህ ጊዜ ውስጥ ራሳቸውን ቤተ ክርስቲያንን ለማጥፋት የሚመኙትን ያህል ምናልባትም ከዚያ በላይ ቤተ ክርስቲያንን የሚጠሉ “ኢትዮጵያውያን ፈረንጆችን” ማፍራት ችለዋል። እነዚህ ከውጪ የሚላክላቸውን አጀንዳና ፍርፋሪ ተቀብለው በውስጥ ሆነው ቤተ ክርስቲያንን ያጠቃሉ። Read more

ለአገራችን ኢትዮጵያ ሰላምን ስጣት

ለአገራችን ኢትዮጵያ ሰላምን ስጣት

ለአገራችን ኢትዮጵያ ሰላምን ስጣት

ለአገራችን ኢትዮጵያ ሰላምን ስጣት

ሊቀ ነቢያት ሙሴ እስራኤላውያን ከአሕዛብ ነገሥታት ጋር ጦርነት በሚያደርጉበት ወቅት ወንድሞቻችሁ ወደ ጦርነት ሔደው እናንተ ከቤታችሁ ተቀምጣችኋል ሲላቸው “እኛ ባሪያዎችህ ሁላችን ጋሻ ጦራችንን ይዘን በእግዚአብሔር ፊት ጌታችን እንደተናገረ ወደ ጦርነት እንሔዳለን” (ዘኁ. ፴፪፡፳፯) የሚል መልስ ሰጥተውታል። በዓለም ላይ ሰላም ሲታጣ  አገራት ሰላም አስከባሪ ኃይል በመላክ ሰላምን በፈረስ አንገት፣ በጦር አንደበት ሊያመጧት ይሻሉ። የተከሠተውን የሰላም እጦት ወደ ነበረበት ለመመለስ ጦርነት ያውጃሉ። ሰላምን የሚሹ ሁሉ ለጦርነት እንዲዘጋጁ ዐዋጅ ይነግራሉ። ሰላም የጦርነት አለመኖር ቢሆንም የሚለካው በውጤቱ ነውና የተባለው ሰላም እስከሚመጣ ሕዝቡ በጦርነት ይሳተፋል። ይህ የዕለት ከዕለት የየአገራት አነዋወር መገለጫ ነው። Read more

ጦርነቱን ወደ ሰላም በማሸጋገር ምድሪቱንም፣ ትውልዱንም ማሳረፍ ከሁሉም ወገን ይጠበቃል

ጦርነቱን ወደ ሰላም በማሸጋገር ምድሪቱንም፣ ትውልዱንም ማሳረፍ ከሁሉም ወገን ይጠበቃል

ጦርነቱን ወደ ሰላም በማሸጋገር ምድሪቱንም፣ ትውልዱንም ማሳረፍ ከሁሉም ወገን ይጠበቃል

ጦርነቱን ወደ ሰላም በማሸጋገር ምድሪቱንም፣ ትውልዱንም ማሳረፍ ከሁሉም ወገን ይጠበቃል

የቅድስት ቤተ ክርስቲያን ተቀዳሚ ተግባር ሐዋርያዊ አገልግሎትን ማከናወን ቢሆንም የአገር ሰላም እንዲሰፍን የመሪነት ሚናስትጫወት ኖራለች። የምንገኝበት ዘመንም ከእስከ አሁኑ የበለጠ የሰላም ሐዋርያ መሆንን የሚጠይቅ ነው። እንኳን ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በኢትዮጵያ ጉዳይ ይመለከተኛል የሚል አካል ሁሉ ሰላም የሚሰፍንበትን መንገድ መፈለግ ከሚያስፈልግበት ደረጃ ላይ እንገኛለን። የቅድስት ቤተ ክርስቲያን የሰላም አምባሳደርነት ለአንድ ወገን ያደላ ሳይሆን የሁሉም እናትነት መሆኗን በተግባር መግለጥ ይገባዋል። Read more

ከአዲስ ተሿሚዎች የሚጠበቅ ተግባርና ኃላፊነት

ከአዲስ ተሿሚዎች የሚጠበቅ ተግባርና ኃላፊነት

ከአዲስ ተሿሚዎች የሚጠበቅ ተግባርና ኃላፊነት

ከአዲስ ተሿሚዎች የሚጠበቅ ተግባርና ኃላፊነት

ሥርዓተ ሲመተ ኤጲስ ቆጶሳት መንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ሐምሌ 09 2015 ዓ.ም

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለመጀመሪያ ጊዜ የራሷ ልጆች ኤጲስ ቆጶስነት እንዲሾሙላት ባደረገች ጊዜ የተፈጸመውን መንፈሳዊ ተግባር በዘመኑ ታትሞ የወጣው ብርሃንና ሰላም ጋዜጣ የዘገበው “አመራረጡ ግን በዕጣ እንዲሆን ምክር ተቈርጦ ስለነበር በዕጣው ላይ ሰባት ቀን ሙሉ በቤተ ክርስቲያን ጸሎት እየተጸለየበት እና ቅዳሴ እየተቀደሰበት ቆይቶ ለአምስቱ መምህራን ዕጣ ወጣላቸው። ስማቸውም መምህር ደስታ፣ መምህር ኃይለ ማርያም፣ መምህር ወልደ ኪዳን፣ መምህር ኃይለ ሚካኤል ናቸው። አምስተኛው ግን ወደ ግብፅ አልወረዱም” በማለት ነበር (ብርሃንና ሰላም ሰኔ 6 ቀን 1921 ዓ.ም፣ ገጽ 189)። Read more

‹‹እንደ ዳኛ ሳይሆን እንደ ጳጳስ አስተዳድር››

‹‹እንደ ዳኛ ሳይሆን እንደ ጳጳስ አስተዳድር››

‹‹እንደ ዳኛ ሳይሆን እንደ ጳጳስ አስተዳድር››

‹‹እንደ ዳኛ ሳይሆን እንደ ጳጳስ አስተዳድር››

ቅዱስ አምብሮስ በቅድስናቸው፣ በተጋድሏቸው ከሚጠቀሱ የምዕራብ ቤተክርስቲያን አባቶች መካከል አንዱ ነው፡፡ ገና ወደ ክርስትና ከመምጣቱ አስቀድሞ በሰሜን ኢጣልያ የምትገኘው ሜሎና የተባለች ግዛት ተሹሞ ነበር፡፡ ሹመቱን የሰማ ከእርሱ የበላይ አስተዳዳሪ የነበረ ሹም ‹‹እንደ ዳኛ ሳይሆን እንደ ጳጳስ አስተዳድር›› በማለት በመልካም ሁኔታ እንዲያስተዳድር መከረው፡፡ የዚህ ሀገረ ገዥ ምክር ገና ከኢጥሙቃን ወገን የነበረውን የአምብሮስን መጻኢ ዕጣ ፈንታ የተናገረ ትንቢት እንደ ነበር ይነገራል፡፡ እርሱም በተሾመበት ቦታ በሚያስገርም ሁኔታ፣ እጅግ በበዛ ቅንነትና ፍትሐዊነት አስተዳደረ፡፡ በሚላኖ መንበር የነበረው አርዮሳዊ ጳጳስ ሲሞት ተተኪውን በመምረጥ ሂደት በሕዝቡ መካከል ከፍተኛ ረብሻ ተነሣ፡፡ አገረ ገዥው አምብሮስ ሁከቱን ለማብረድ ሕዝቡን በሚያረጋጋበት ጊዜ አንድ ሕፃን ልጅ ድንገት ‹‹አምብሮስ ጳጳስ መሆን አለበት!›› በማለት በጩኸት ተናገረ፡፡ ሕዝቡ ተገርሞ የሕፃኑን ድምፅ የእግዚአብሔር መልእክት አድርጎ ተቀበለው፡፡ Read more

የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን

የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ታሪካችን – ክፍል ሦስት

የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን

የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን

 

ባለፉት ሁለት ተከታታይ ጽሑፎች የኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ታሪካችን በፈተና የተከበበ መሆኑን አንሥተናል። ዐፄ ኃይለ ሥላሴ ቅድስት ቤተክርስቲያን ከራሷ መነኰሳት ጳጳሳትን እንድትሾም ያደረጉት አስተዋጽዖ ከፍተኛ ቢሆንም በራሳቸው ወርድ ለመስፋት ያደርጉት የነበረው ጣልቃ ገብነት ደግሞ አሁን ለደረስንበት ችግር እንደ አንድ ምክንያት ሊጠቀስ የሚችል ነው።  ኢትዮጵያውያን ጳጳሳት እንዲሾሙ ያደረጉት ተጋድሎ በሌላ በኩል አባቶች መንግሥት ካከልን ብለው እንዲዘናጉ ሳያደርግ አልቀረም። በ፲፱፻፳፩ዓ.ም ከራሳችን መነኰሳት ኤጲስ ቆጶሳት እንደተሾሙ ሊቀጳጳሱና ኤጲስ ቆጶሳቱ ጉባኤ አድርገው በመምከር ሊያደርጉት የሚገባውን የሀገረ ስብከት ምደባ ንጉሠ ነገሥቱ መፈጸማቸው ለጉዳዩ ትኩረት ለመስጠት ጠቅሟል የሚል አካል ቢኖርም በየዘመናቱ ለተነሡ ባለሥልጣናት መንገድ ቀይሰዋል።

 

Read more

የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን

የኢጲስ ቆጶሳት ታሪካችን ክፍል ሁለት

የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን

የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ኢጲስ ቆጶሳት ሢመት ታሪክ ውስብስብ መሆኑ የሚታወቅ ነው። ውስብስብ እንዲሆን ያደረገው በአንድ በኩል ግብፆች ሢመቱን ለጊዜያዊ ጥቅም ማግኛ በማድረግ ፓትርያርኮች ከራሳችን መነኰሳት እንድንሾም ቢፈቅዱ እንኳ የእስልምና እምነት ተከታይ መሪዎቻቸው መከልከላቸው ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ የአገራችን ነገሥታት በአዎንታዊ መንገድም ቢሆን ጣልቃ መግባታቸው “መንግሥትና ሃይማኖት የተለያዩ ናቸው” በማለት በዐደባባይ ምለው የሚገዘቱ የዘመናችን መሪዎችም በተግባር ቤተ ክርስቲያንን ለማዳከም በእጅጉ “የቤተ ክርስቲያን ጉዳይ ፈጻሚ” ሆነው እንዲታዩ በር የከፈተ በመሆኑ ነው። Read more