የነገረ ሰብእ ትምህርት ጉድለት የወለደው አገራዊ ቀውስ

ከወርቃማው ሕግ አትንሸራተቱ (የነገረ ሰብእ ትምህርት ጉድለት የወለደው አገራዊ ቀውስ ክፍል ሁለት)

የነገረ ሰብእ ትምህርት ጉድለት የወለደው አገራዊ ቀውስ

የነገረ ሰብእ ትምህርት ጉድለት የወለደው አገራዊ ቀውስ

የተከበራችሁ የማኅበራዊ ሚዲያችን ተከታታዮች አስቀድምን ባስነበብነው የዚህ ጽሑፍ የመጀመሪያ ክፍል ሰው በእግዚአብሔር አርአያ እና ምሳሌ የተፈጠረ የፍጥረታት ንጉሥ፣ ከሌሎች ፍጥረታት ተለይቶ ዐዋቂ እና ሕያውነት ያለው፣ በፍጥረታት ላይ የሠለጠነ ባለጸጋ ፍጡር መሆኑን አቅርበን ነበር። በዚህም ምክንያት ሰው ነጻ ፈቃዱን ተጠቅሞ ሲጠፋ ከሦስቱ አካላት አንዱ ወልድ “እስመ በፈቃዱ፣ ወበሥምረተ አቡሁ ወመንፈስ ቅዱስ መጽዐ አድኀነነ” እንደ ተባለው ሰው ሆኖ ሰውን ከውድቀት አነሣው። ዘጠና ዘጠኙን ነገደ መላእክት ትቶ አንዱን ነገድ ሰውን ለመፈለግ ሰው የሆነው ለሰው ካለው ጽኑ ፍቅር የተነሣ ነው። Read more

ብሔር ተኮር ሃይማኖታዊ ስብከት

ብሔር ተኮር ሃይማኖታዊ ስብከት

ብሔር ተኮር ሃይማኖታዊ ስብከት

ብሔር ተኮር ሃይማኖታዊ ስብከት

ቤተ ክህነቱ ታሟል

ጎሣን መሠረት ያደረገው የሀገራችን ፖለቲካ ኢትዮጵያዊነት ዕሴቶችን በማፈራረስ ሀገር የቆመበትን መሠረት ለመናድ መዶሻውን ካነሣ ምእተ ዓመት ሊያስቆጥር የመጨረሻው ሩብ ክፍለ ዘመን ብቻ ቀርቶታል፡፡ በሀገረ ምሥረታው ሒደት ምትክ የለሽ ሚና የተጫወተችውን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጥፋቱ ሰለባ የሆነችው ገና ከጅምሩ ነው፡፡ የቤተ ክርስቲያን አሐቲነት አደጋ ላይ የወደቀበት እና በከፋ የፈተና ማዕበል እየተናጠች የምትገኝበት ዘመን ላይ መሆናችን ፀሐይ የሞቀው እውነት ነው፡፡ Read more

የነገረ ሰብእ ትምህርት ጉድለት የወለደው አገራዊ ቀውስ

የነገረ ሰብእ ትምህርት ጉድለት የወለደው አገራዊ ቀውስ

የነገረ ሰብእ ትምህርት ጉድለት የወለደው አገራዊ ቀውስ

የነገረ ሰብእ ትምህርት ጉድለት የወለደው አገራዊ ቀውስ

በቤተ ክርስቲያን ትምህርት ነገረ ሰብእ (አንትሮፖሎጂ) አንደኛው የጥናት ዘርፍ ነው። ይህ የጥናት ዘርፍ ስለ ሰው አፈጣጠርና ክብር የሚናገር ነው። ስለ ፍጥረት አመጣጥ የሚናገረው የመጽሐፍ ቅዱስ የመጀመሪያው መጽሐፍ ኦሪት ዘፍጥረት ሰው በእግዚአብሔር አርአያና ምሳሌ የተፈጠረ ክቡር ፍጡር መሆኑን ይነግረናል። ሊቀ ነቢያት ሙሴ ስለ አፈጣጠሩ ሲተርክልንም “እግዚአብሔርም አለ፤ ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌያችን እንፍጠር፤ የባሕር ዓሦችንና የሰማይ ወፎችን፣ እንስሳትንና ምድርን ሁሉ፣ በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ፡ እግዚአብሔርም ሰውን በመልኩ ፈጠረ፤ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው፤ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው” (ዘፍ. ፩፡፳፮-፳፯) ይለናል። የሚወዱትን እንግዳ ሁሉን አዘጋጅቶ እንደሚጠሩት እግዚአብሔርም ለሰው የሚያስፈልገውን ሁሉ አስቀድሞ ካዘጋጀ በኋላ ሰውን የፍጥረት መደምደሚያና መካተቻ አድርጎ ፈጥሮታል። እግዚአብሔር ሌሎች ፍጥረታትን በኀልዮ (በማሰብ) እና በነቢብ (በመናገር) ሲፈጥራቸው ሰውን ግን በእጁ ሠርቶታል። “እግዚአብሔር አምላክ ሰውን ከምድር አፈር አበጀው፤ በፊቱም የሕይወት እስትንፋስን እፍ አለበት፤ ሰውም ሕያው ነፍስ ያለው ሆነ” (ዘፍ. ፪፡፯) የተባለው ለዚህ ነው። ስለሆነም ሰው ክብሩና ልእልናው ከፍ ያለ ነው። Read more

የዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ዮናታን እስር

የዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ዮናታን እስር

የዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ዮናታን እስር

የዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ዮናታን እስር

ሊቀ ጳጳስ ዮናታን በዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የተልኪና ብራስላቭ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ናቸው። የሀገሪቱ መንግሥት ዩክሬን የምትመራበትን ወንጀለኛ መቅጫ ሕግ አንቀጽ 109፣ 110፣ 161 እና 436 (2) በመጥቀስ በአራት ወንጀሎች ጠርጥሬያቸዋለሁ በማለት ክስ ይመሠርትባቸዋል። ጉዳዩን በአግባቡ ለመረዳት ሊቀ ጳጳሱ የተከሰሱባቸው የወንጀል ሕጉ ድንጋጌዎች ምን ምን እንደሚሉ አስቀድመን እንመለከታለን።

  • አንቀጽ 109 በዐመጽ ለውጥ ለማምጣት ወይም ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ለማስወገድ ወይም በኃይል ሥልጣን ለመያዝ የሚፈጸሙ ተግባራት
  • አንቀጽ 110 – የዩክሬንን ሉዓላዊ የግዛት ወሰን ማለፍ ወይም ዳር ድንበሯን ለመለወጥ አስቦ መሥራት
  • አንቀጽ 161 – ዘርን፣ ሃይማኖትን እና ዜግነትን መሠረት በማድረግ ልዩነት መፍጠር
  • አንቀጽ 463 (2) – የጦርነት ፕሮፖጋንዳ መንዛት (ሩሲያ በዩክሬን ላይ የፈጸመችውን የኃይል ወረራ አይቀበሉም፣ ለሕጋዊነቱ ዕውቅና ሰጥተዋል፤ የሩሲያ ወታደሮችን አድንቀዋል) የሚሉ ናቸው።

Read more

“ክርስቲያኖች መተት አደረጉብን”

“ክርስቲያኖች መተት አደረጉብን”

“ክርስቲያኖች መተት አደረጉብን”

“ክርስቲያኖች መተት አደረጉብን”

መቼም በየዘመኑ የማይሰማ ጉድ የለም። ከመጀመሪያው መቶ ክፍለ ዘመን አንሥቶ በየሀገሩ ይኖሩ የነበሩ አረማውያን እና አሕዛብ ክርስቲያኖችን ተከራክረው ማሸነፍ እንደማይቻላቸው ሲረዱ አንድ መላ ዘይደው ነበር። ይኸውም “ክርስቲያኖች የሰው ሥጋ ይበላሉ” ብለው በማስወራት ስለክርስትና የማያውቁ የሰው ልጆች እንዲርቁ በሌላ በኩልም ሃይማኖቱ ሕገ ወጥ ተብሎ ከምድረ ገጽ እንዲጠፋ ማስደረግ ነበር። ይህም ሐዋርያት ወንጌልን ለመላው ዓለም ለማዳረስ በሚሰማሩባቸው ቦታዎች ሁሉ እንደ በግ እንዲታረዱ የሱ ምክንያት ነበረው። የአረማውያኑ አሳብ መከራውን ተሰቅቀው ሌሎች እንዲሸሿቸው ማድረግ ቢሆንም ውጤቱ ግን በተቃራኒው ነበር። Read more

እነርሱ እያቃጠሉ እኛ ስንሠራ አንኖርም

እነርሱ እያቃጠሉ እኛ ስንሠራ አንኖርም

ዘመናችን “መታዘዝ እንደ ድካም፣ ትሕትና እንደ ውርደት፣ ራስን መግዛት ራስን እንደ መጨቈን፣ በሥርዓት ማደር እንደ ኋላ ቀርነት፣ ክህነታዊ ተዋረድን የጠበቀ አገልግሎት ዘመን እንዳለፈበት የጭቆና መሣሪያ፣ ሃይማኖተኛነት እንደ ተራ ወግ አጥባቂነት ተፈርጆ ይዘመትበታል፡፡ ነባር ሃይማኖትን መቃወምን እንደ ሃይማኖት የያዘ መስተጻርርነት አየሩን ሞልቶታል” በማለት በአማን ነጸረ የጻፈው በተግባር ተገልጦ የሚታይበት ነው። ፀረ -ኦርቶዶክሶችም ይባል አክራሪዎች በኦርቶዶክሳውያን እንደሚሸነፉ ሲረዱ እግር ላይ ወድቀው የሚለምኑት በኦርቶዶክሳውያን መልካም ዕሴት ላይ ተሸጋግረው አዘናግተው ለማጥቃት ወይም ጊዜ ለመግዛት እንጂ በሚልኩት ሽምግልናም ሆነ በሚያቀርቡት ተማጽኖ አምነውበት አይደለም።
የአክራሪዎች መርሕ ራስ ብቻ ደኅና የሚል ነው። የራሳቸው ደኅንነት ከሌላው ደኅንነት ጭምር እንደሚመነጭ አመዛዝነው መረዳት የሚችሉበት አእምሮ የተነሣቸው ናቸው። መደጋገፍ የሚባለው አብሮ የመኖር ባህል፣ መከባበር የሚሉት መልካም ዕሴት አይገባቸውም። ሁሉ ነገር የእኛ፣ ሁሉን እኛ ይዘነው ሌላው ከገጸ ምድር ይጠፋ የሚል ነው። ለቀጣይ ትውልድ ማሰብ የሚባል ነገር አያውቁም። ሌላው የለፋበትን ነጥቆ መውሰድ ወይም ማውደም ሃይማኖት ብለው የያዙት እኩይ ድርጊት ነው። እግዚአብሔር የፈጠረውን ትውልድ በማጥፋት “የፈጠርከውን አጠፋንልህ” ብለው ለባለቤቱ ሪፖርት የሚያቅርቡ ናቸው። እንዲህ ያለው መረን የለቀቀ አስተሳሰብ ክቡር የሆነውን ፍጡር ከእንስሳ ተራ የሚያስመድብ ነው። Read more

ከደቂቀ እስጢፋኖስ እስከ መንበረ ሰላማ

ከደቂቀ እስጢፋኖስ እስከ መንበረ ሰላማ

ከደቂቀ እስጢፋኖስ እስከ መንበረ ሰላማ

ከደቂቀ እስጢፋኖስ እስከ መንበረ ሰላማ

የተከበራችሁ አንባብያን የዚህን ጽሑፍ የመጀመሪያ የሆነውን እና አቡነ ተክለ ሃይማኖትን በተመለከተ ተሐድሶ መናፍቃን እና ተስፈንጣሪ ፖለቲከኞች የሚያነሷቸውን የፈጠራ ድርሰቶች መነሻ ምክንያት የሚያስነብበውን ጽሑፍ ለንባብ ማብቃታችን የሚታወቅ ነው። ቀጣዩን ክፍል ደግሞ እንደሚከተለው አቅርበነዋል። መልካም ንባብ፡-

ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ

በመካከለኛው ዘመን ለቤተ ክርስቲያን መልካም ካደረጉ ነገሥታት አንዱ ዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ ነው። ንጉሡ አገሪቱን ለሁለት ሊከፍል ጫፍ ደርሶ የነበረውን የቤተ ተክለ ሃይማኖት እና የቤተ ኤዎስጣቴዎስ ጉዳይ መፍትሔ በመስጠት ሰላም እንዲወርድ አድርጓል። ጉዳዩ እንዲህ ነው። በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርሰቲያን በሐዋርያዊ አገልግሎታቸው የሚታወቁት የአቡነ ተክለ ሃይማኖት ገዳም መነኰሳት እና የአባ ኤዎስጣቴዎስ ተከታዮች ልዩነት ፈጥረው ነበር። የልዩነቱ ምክንያት ቤተ ተክለ ሃይማኖቶች መከበር የሚገባት ሰንበተ ክርስቲያን እንጂ ሰንበተ አይሁድ መከበር የለባትም ሲሉ ኤዎስጣቴዎሳውያን ደግሞ ቅዳሜም፣ እሑድም መከበር አለባቸው የሚል አቋም ያዙ። በዘመኑ የነበሩ ነገሥታት አቡነ ተክለ ሃይማኖትን ያከበርን መስሏቸው የእርሳቸውን ገዳም መነኰሳት አሳብ ደግፈው ቤተ ኤዎስጣቴዎሳውያንን መግፋት በመጀመራቸው ልዩነቱ እየሰፋ ሄደ። Read more

ከደቂቀ እስጢፋኖስ እስከ መንበረ ሰላማ

ከደቂቀ እስጢፋኖስ እስከ መንበረ ሰላማ

ከደቂቀ እስጢፋኖስ እስከ መንበረ ሰላማ

ከደቂቀ እስጢፋኖስ እስከ መንበረ ሰላማ

አባ እስጢፋኖስን እና ተከታዮቹንበተመለከተ ብዙ ይጻፋል፣ ይነገራል። የእርሱ እና የተከታዮቹ ጉዳይ ማንም እንደፈለገ ለመዘወር የተመቸ ነው። ከትግራይ ክልል የተነሡ ተስፈንጣሪ ፖለቲከኞች ባላንጣችን የሚሉትን ሸዋን ለመተቸት ይጠቅሱታል። በክልሉ ኑፋቄያቸውን ለመዝራት ፈልገው ያልተሳካላቸው ተሐድሶ መናፍቃን በዕውቀቱ አቻ የሌለው፣ በአስተምህሮው እንከን የማይገኝበት አስመስለው ያቀርቡታል። ቤተ ክርስቲያኗን በዘር ለመከፋፈል የሚደክሙ አካላት አርአያነቱን እንከተል በማለት የፈጣራ ድርሰት ጽፈው ያነቡለታል። እንደ አባ እስጢፋኖስ ያለ ምግባረ ብልሹ ራሱን ኮፍሶ ሌላውን ስለሚያናንቅ እንዲህ ያለው ምግባር የመናፍቃንመለያ መሆኑን መረዳት ከተደጋጋሚ ጥፋት ይታደጋል። Read more

የትግራይ ቤተ ክህነት እንቅስቃሴ ለተሐድሶ መናፍቃን ሰርግና ምላሽ

የትግራይ ቤተ ክህነት እንቅስቃሴ ለተሐድሶ መናፍቃን ሰርግና ምላሽ

የትግራይ ቤተ ክህነት እንቅስቃሴ ለተሐድሶ መናፍቃን ሰርግና ምላሽ

የትግራይ ቤተ ክህነት እንቅስቃሴ ለተሐድሶ መናፍቃን ሰርግና ምላሽ

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለሀገር ካበረክተችው አስተዋጽኦ አንዱ የሀገር አንድነት ምክንያት ሆና መኖሯ ነው። ለዚህም ነው ኢትዮጵያን ማዳከም የሚፈልጉ ኃይሎች ሁሉ መጀመሪያ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን ማዳከምን ዋና አጀንዳቸው የሚያደርጉት። በተለይም ከ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ጀምሮ ወደ ኢትዮጵያ የመጡት ሚስዮናውያን ቤተ ክርስቲያንን በማጥፋት ኢትዮጵያን መረከብ አጀንዳቸው ካደረጉ ከአራት መቶ በላይ ዘመናትን አስቈጥረዋል። በዘህ ጊዜ ውስጥ ራሳቸውን ቤተ ክርስቲያንን ለማጥፋት የሚመኙትን ያህል ምናልባትም ከዚያ በላይ ቤተ ክርስቲያንን የሚጠሉ “ኢትዮጵያውያን ፈረንጆችን” ማፍራት ችለዋል። እነዚህ ከውጪ የሚላክላቸውን አጀንዳና ፍርፋሪ ተቀብለው በውስጥ ሆነው ቤተ ክርስቲያንን ያጠቃሉ። Read more

ለአገራችን ኢትዮጵያ ሰላምን ስጣት

ለአገራችን ኢትዮጵያ ሰላምን ስጣት

ለአገራችን ኢትዮጵያ ሰላምን ስጣት

ለአገራችን ኢትዮጵያ ሰላምን ስጣት

ሊቀ ነቢያት ሙሴ እስራኤላውያን ከአሕዛብ ነገሥታት ጋር ጦርነት በሚያደርጉበት ወቅት ወንድሞቻችሁ ወደ ጦርነት ሔደው እናንተ ከቤታችሁ ተቀምጣችኋል ሲላቸው “እኛ ባሪያዎችህ ሁላችን ጋሻ ጦራችንን ይዘን በእግዚአብሔር ፊት ጌታችን እንደተናገረ ወደ ጦርነት እንሔዳለን” (ዘኁ. ፴፪፡፳፯) የሚል መልስ ሰጥተውታል። በዓለም ላይ ሰላም ሲታጣ  አገራት ሰላም አስከባሪ ኃይል በመላክ ሰላምን በፈረስ አንገት፣ በጦር አንደበት ሊያመጧት ይሻሉ። የተከሠተውን የሰላም እጦት ወደ ነበረበት ለመመለስ ጦርነት ያውጃሉ። ሰላምን የሚሹ ሁሉ ለጦርነት እንዲዘጋጁ ዐዋጅ ይነግራሉ። ሰላም የጦርነት አለመኖር ቢሆንም የሚለካው በውጤቱ ነውና የተባለው ሰላም እስከሚመጣ ሕዝቡ በጦርነት ይሳተፋል። ይህ የዕለት ከዕለት የየአገራት አነዋወር መገለጫ ነው። Read more