የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት - በኢ/ኦ/ተ/ቤ የመንበረ ፓትርያርክ ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ አንድነቱ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ተቋማዊ ራእይ፣ ተልእኮ
      • መዋቅራዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቋማዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማስፈጸሚያ
    • ስልታዊ እቅድ 2018 – 2021 ዓ/ም
  • ሥርዓተ ትምህርት
    • መሠረታዊ መረጃዎች
    • የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት አደረጃጀት መመሪያ
    • የሥርዓተ ትምህርቱ መመማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
    • የሥርዓተ ትምህርቱ ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ /ካሌንደር
    • የመምህራን ሥልጠና እና መልእክቶች
    • መጻሕፍቱን ለማግኘት እና ተጨማሪ መረጃ
    • ልዩ ልዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች
  • ፕሮጀክቶች
  • መዝሙረ ማኅሌት
    • የመስከረም ወር መዝሙሮች
      • የዮሐንስ መዝሙር
      • የመስቀል መዝሙሮች
      • የብዙኃን ማርያም መዝሙር (መስከረም ፳፩ )
      • የዘመነ ጽጌ መዝሙር
    • የጥቅምት ወር መዝሙሮች
      • የአብርሃ ወአጽብሐ መዝሙር (ጥቅምት 4 ቀን)
    • የኅዳር ወር መዝሙሮች
      • የቅዱስ ሚካኤል መዝሙር (ኅዳር 12 ቀን)
    • የጥር ወር መዝሙሮች
      • የዘመነ ጥምቀት መዝሙር
      • የቃና ዘገሊላ መዝሙር (ጥር 12 ቀን)
    • የመጋቢት ወር መዝሙሮች
      • የወርኃ ጾም መዝሙሮች
      • የሆሣዕና መዝሙራት
      • የሰሙነ ሕማማት መዝሙሮች
  • ዜና
    • አጫጭር ዜናዎች
    • ዝርዝር ዜናዎች
    • ወቅታዊ መረጃዎች
    • ማስታወቂያ
      • የሰንበት ትምህርት ቤቶች መጻሕፍት እንግሊዝኛ ትርጉም ሥራ ተሳትፎ ጥሪ
  • ያግኙን
  • ቋንቋ
    • ትግርኛ
    • Afaanoromo
  • Menu Menu

መዋቅሩ ለወንጌል ወይስ ወንጌሉ ለመዋቅሩ?

መዋቅሩ ለወንጌል ወይስ ወንጌሉ ለመዋቅሩ?

መዋቅሩ ለወንጌል ወይስ ወንጌሉ ለመዋቅሩ?

ኤፍሬም እንዳለ የተባለ ደራሲ “እንጨዋወት” በሚል ርእስ ያዘጋጀው ትኩረቱን ማኅበራዊ ሂስ ላይ ባደረገው መጽሐፍ አንድ ታሪክ እናገኛለን። ታሪኩ እንዲህ ነው። አንድ ድርጅት ከከተማ ወጣ ባለ ቦታ ያከማቻቸው አሮጌ መኪናዎች፣ የወላለቁ ብረታ ብረቶች እና ከጥቅም ውጭ የሆኑ የተለያዩ ቁሰቁሶች ነበረው፡፡ ክምችቱ ያለ ጥበቃ ለረጅም ጊዜ ቆይቷል፡፡ በኋላ ግን የድርጅቱ ባለ ሥልጣናት መጠበቅ አለበት ብለው ስላመኑ ሁለት የጥበቃ ሠራተኞች እንዲቀጠሩ ወሰኑ።

 

ከጥቂት ጊዜ በኋላ ጥበቃዎቹ በሰዓት መግባት መውጣታቸውን ከዋናው መሥሪያ ቤት ሆኖ በርቀት መከታተል እንዳልተቻለ ዘገባ ቀረበ፡፡ እነርሱን በፈረቃ የሚከታተሉ ሁለት ሰዎች ተቀጠሩ፡፡ ከቆይታ በኋላ ለአራቱ ሠራተኞች ደመወዝ ከፋይ እንደሚያስፈልግ ታመነበትና ተቀጠረ፡፡ ከዚያም የሰው ኃይል አስተዳደር መኖር አለበት ተብሎ እርሱም ተቀጠረ፡፡ የሰው ኃይል አስተዳደሩ ጸሐፊ ስላስፈለገው ጸሐፊ ተጨመረ፡፡ ይህን ሁሉ ያለ ሥራ አስኪያጅ ማስተዳደር እየከበደ ስለመጣ ዋና ሥራ አስኪያጅ ተሾመለት፡፡ እንዲህ እንዲህ እያለ ቀስ በቀስ ብዙ ሠራተኞች ያለው ድርጅት ሆነ፡፡

 

ከተወሰነ ጊዜ በኋላ ዋናው ድርጅት ትልቅ በጀት የሚጠይቅ ነገር ግን ምንም ገቢ የማያመነጭ ድርጅትን ተሸክሞ መቀጠል እየከበደው ሄደ፡፡ ስለዚህ የሠራተኛ ቅነሳ መደረግ እንዳለበት ተወሰነ፡፡ የሚገርመው መጀመሪያ እንዲቀነሱ የተወሰነባቸው መጀመሪያ የተቀጠሩት የጥበቃ ሠራተኞች መሆናቸው ነው፡፡ ለድርጅቱ ህልውና ምክንያት የሆኑት እነርሱ መሆናቸው ተዘነጋ፡፡ ብዙ ሰው የያዘው ድርጅት ዋና ዓላማ የተከማቸውን አሮጌ ቁሳቁስ መጠበቅ ነበር፡፡ ኋላ ግን የዓላማው አስፈጻሚዎች ዋጋ ተረሳና ጥበቃዎቹ ቀዳሚ ተባራሪ ሆኑ፡፡

 

በቤተ ክህነት ሲፈጸም የሚታየው ነገር ከዚህ ድርጅት ጋር ተመሳሳይነት አለው፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ለሁለት ሺሕ ዘመናት ሁል ጊዜ አዲስ  የሆነውን ቅዱስ ወንጌልን እየሰበከች ኖራለች፡፡ ቤተ ክርስቲያን ከጥንትም ለወንጌል አገልግሎት የተዘጋጀ ጽኑ ፍቅር እና መንፈሳዊ ቁርጠኝነት የሚታይበት ሥርዐት ነበራት፡፡ ነገር ግን ዘመናዊ የቤተ ክህነት መዋቅር ከመጀመሪያው ኢትዮጵያዊ ፓትርያርክ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ባስልዮስ ዘመን በኋላ ነው መደበኛ በሆነ አደረጃጀት የተዋቀረው ( ስማቸው ንጋቱ፣ 2013 ዓ.ም፣ 199)፡፡ ቤተ ክህነቱ የተዋቀረው ወንጌለ መንግሥትን ለሰው ልጅ ሁሉ ለማድረስ ነው፡፡ መዋቅሩ ያስፈለገው ቤተ ክርስቲያን ለቆመችለት ዋነኛ አገልግሎት አጋዥ እንዲሆን ነው።

 

ዛሬ ቤተ ክህነቱን ከተቀዳሚው የቤተ ክርስቲያን ተልእኮ ጋር እንዳይራመድ እንቅፋት የሚሆኑ ምንደኞች ወርረውታል፡፡ ወንጌልን ማስተማር የቤተ ክርስቲያን ዋነኛ ተልእኮዋ መሆኑን ከመጻሕፍት ሆድ፣ ከመዛግብት ገጽ እናገኘው እንደ ሆነ እንጂ በቤተ ክህነት እንዲያገለግሉ ከተመደቡ ሰዎች ልብ ውስጥ የተጻፈ አይመስልም፡፡ ሹመት፣ ደመወዝ፣ መኪና እና ቤት የሚያማርጡ፣ የምእመናን ቍጥር በቅሰጣና በስደት መቀነሱ የማያስጨንቃቸው ወረውታል፡፡ ቤተ ክርስቲያንን የሚፈልጓት ለደመወዛቸው እንጂ  እንዴት ውላ እንዳደረች አይጨነቁም። ለምእመናን የሕይወት ቃል የሚመገቡባት ሰማያዊ መዓድ፣ የቃልን ወተት የሚጠጡባት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለምንደኞች የማትነጥፍ  ጥገት ሆናለች።

 

ቤተ ክርስቲያን በምድር ያለች የእግዚአብሔር መንግሥት ስትሆን ተልእኮዋም  የሕይወትን ቃል ለዓለም ሁሉ ማዳረስ ነው፡፡ የሰሙት እንዲያምኑ፣ ያመኑት ከመንፈስ ቅዱስ ተወልደው፣ በመልካም ምግባርና ትሩፋት አጊጠው የሰማያዊት ኢየሩሳሌም ወራሾች እንዲሆኑ ማጽናት። ከአናጎንስጢስ ጀምሮ እስከ ጳጳሳቱ “በጎቼ፣ ጠቦቶቼና ግልገሎቼ” በማለት ጌታችን የጠራቸው ምእመናንን መጠበቅ ያለባቸው መሆኑን ረስተውታል።

 

ለቤተ ክህነቱ መዋቅር አንቀሳቃሽ የሆኑ ምእመናን ተረስተዋል፡፡ የሚፈለጉት ጥላ ሲዘቀዘቅ ገንዘብ እንዲሰጥ ብቻ ነው፡፡ ምእመኑን የሚፈለጉት የደብሩ አለቃ ጓዳ ወይም  በአስተዳደር መዋቅር ውስጥ የተሰገሰጉ የሥም አገልጋዮች ኪስ ሲራቆት ነው። በጎቹን፣ ጠቦቶቹንና ግልገሎቹን ዓለም ያስነሣችው ማዕበል ሲያናውጣቸው ፣ ዕረፍት የለሽ ሩጫ የሚጠይቀው የዓለም ኑሮ ሥነ ልቡናቸውን ሲያውከው ፈጥነው ደርሰው የሚያረጋጉ ጥቂት ናቸው፡፡ ከልጆቻቸው ጉሮሮ ነጥቀው መባ ሰጥተው፣ ድንጋይ ተሸክመው፣ ባለሥልጣናትን አድሏዊ አሠራር እና ማዋከብ ተቋቁመው በሚተክሏት ቤተ ክርስቲያን በሚሾሙ ሰዎች ምግባረ ብልሽነት፣ ሙዳየ ምጽዋት በሚያራቁቱ ምንደኞች ተማረዋል፡፡

 

ሠራኤ ሕግ በሆነችው ቤተ ክርስቲያን ሕግ አፍራሾች እንደ ሊባኖስ ዛፍ ከፍ ከፍ ብለው ሲታዩ  መንፈሳቸው የሚታወክ ምእመናን ብዙ ናቸው፡፡ በተረበሸ መንፈስ ከአምላካቸው ጋር የኅሊና ሙግት ሲገጥሙ ዐይናቸውን ለጽድቅ በተሰለፉት እውነተኛ ጳጳሳት እና ካህናት ላይ እንዲያደርጉ መንገድ የሚያሳያቸው ከወዴት አለ? በአንድ ሰው ነፍስ መመለስ ታላቅ ደስታ የሚደረግባት የሰማያዊቷ ኢየሩሳሌም አምሳያ የሆነችውን ቤተ ክርስቲያን የሚመሩ ጳጳሳት እንደ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ በመከራቸው ሰዓት አልደረሱላቸውም፡፡ አንዳንድ ካህናት፣ ሰባክያትና ጳጳሳት የሚያሳዩት ምግባር የጎደለው ድርጊት  ብዙዎች ጥያቄ እንዲያነሡ ያደርጋል። የአገልጋዮች ድርቀት በቤተ ክርስቲያን ላይ ከባድ ፈተና ደቅኗል፡፡ ይህ ሁሉ ለምን ሆነ? ብለን መጠየቅ ብቻ ሳይሆን  ወደ ራሳችን በመመልከት ለተበላሸው አሠራር የእያንዳንዳችን ድርሻ ሊኖር እንደሚችል መረዳት  ይኖርብናል፡፡

 

ቤተ ክህነቱ አባቶቻችን በተጓዙበት የጽድቅ ፍኖት በሚጓዙ አገልጋዮች ድርቅ ተመትቷል፡፡ ለዚህ ድርቅ የተዳረግነው እውነተኛ አገልጋዮችን ለማገዝ እና የተበላሸውን አሠራር ለማረም ዳተኛ በመሆኑ ነው።  ችግሮች የበዙት ልጆቿ ግዴለሽነት ምክንያት እንደ ሆነ ማን ያውቃል? ከግዴለሽነት አዚም በመውጣት አገልግሎቱን በአስተማማኝ መሠረት ማቆም ይገባል። ቤተ ክህነትን ከምንደኞች መሻኮቻነት ነፃ ማድረግ የተጣለባቸውን ኃላፊነት በሚገባ የሚወጡ የወንጌል መልእክተኞች ብቻ እንዲያገለግሉበት ማድረግ ከሁሉ ቅድሚያ የሚሰጠው ተግባር ነው።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on LinkedIn
  • Share on Telegram
  • Share by Mail
https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/bete-khnet.jpg 1080 1920 Abenezer Mamushet https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/logo-2-1-300x74-1.png Abenezer Mamushet2023-08-04 22:26:222023-08-04 22:26:22መዋቅሩ ለወንጌል ወይስ ወንጌሉ ለመዋቅሩ?
Search Search

Recent Posts

  • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ
  • ሦስተኛ ዙር የ፲፪ ክፍል ምርቃት መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት ተከናወነ።

Archives

  • April 2026
  • September 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • May 2025
  • April 2025
  • October 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • July 2022
  • June 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
© Ethiopian Orthodox Church Global Sunday School Union | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
  • Link to Youtube
  • Link to Telegram
  • Link to TikTok
Link to: የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን Link to: የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን የኤጲስ ቆጶሳት አሿሿም ታሪካችን Link to: የኢጲስ ቆጶሳት ታሪካችን ክፍል ሁለት Link to: የኢጲስ ቆጶሳት ታሪካችን ክፍል ሁለት የኢጲስ ቆጶሳት ታሪካችን ክፍል ሁለት
Scroll to top Scroll to top Scroll to top