የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት - በኢ/ኦ/ተ/ቤ የመንበረ ፓትርያርክ ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ አንድነቱ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ተቋማዊ ራእይ፣ ተልእኮ
      • መዋቅራዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቋማዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማስፈጸሚያ
    • ስልታዊ እቅድ 2018 – 2021 ዓ/ም
  • ሥርዓተ ትምህርት
    • መሠረታዊ መረጃዎች
    • የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት አደረጃጀት መመሪያ
    • የሥርዓተ ትምህርቱ መመማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
    • የሥርዓተ ትምህርቱ ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ /ካሌንደር
    • የመምህራን ሥልጠና እና መልእክቶች
    • መጻሕፍቱን ለማግኘት እና ተጨማሪ መረጃ
    • ልዩ ልዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች
  • ፕሮጀክቶች
  • መዝሙረ ማኅሌት
    • የመስከረም ወር መዝሙሮች
      • የዮሐንስ መዝሙር
      • የመስቀል መዝሙሮች
      • የብዙኃን ማርያም መዝሙር (መስከረም ፳፩ )
      • የዘመነ ጽጌ መዝሙር
    • የጥቅምት ወር መዝሙሮች
      • የአብርሃ ወአጽብሐ መዝሙር (ጥቅምት 4 ቀን)
    • የኅዳር ወር መዝሙሮች
      • የቅዱስ ሚካኤል መዝሙር (ኅዳር 12 ቀን)
    • የጥር ወር መዝሙሮች
      • የዘመነ ጥምቀት መዝሙር
      • የቃና ዘገሊላ መዝሙር (ጥር 12 ቀን)
    • የመጋቢት ወር መዝሙሮች
      • የወርኃ ጾም መዝሙሮች
      • የሆሣዕና መዝሙራት
      • የሰሙነ ሕማማት መዝሙሮች
  • ዜና
    • አጫጭር ዜናዎች
    • ዝርዝር ዜናዎች
    • ወቅታዊ መረጃዎች
    • ማስታወቂያ
      • የሰንበት ትምህርት ቤቶች መጻሕፍት እንግሊዝኛ ትርጉም ሥራ ተሳትፎ ጥሪ
  • ያግኙን
  • ቋንቋ
    • ትግርኛ
    • Afaanoromo
  • Menu Menu

ዕርገተ ክርስቶስ

“እያዩት ከፍ ከፍ አለ፤ ደመናም ከዓይናቸው ሰውራ ተቀበለችው” ሐዋ. 1÷9

ዕርገት ማለት ወደላይ ከፍ ከፍ ማለት ሲሆን የመሬትን የስበት ኃይል የሚያሸንፍ ከፍታ ነው፡፡ ክርስቶስ ወደ ሰማይ ያረገው የመሬት የስበት ኃይልሳይገድበው ነው፡፡ የክርስቶስ ዕርገት ቀድሞ በትንቢት የተነገረ፤ በሚያምኑት ዘንድ በናፍቆት ሲጠበቅ የቆየ እና በራሱ በጌታችን የተሰበከ ነው፡፡

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለ፴፫ ዓመታት ከሦስት ወራት በምድር ኖሯል፡፡ በ፴ ዓመቱ ተጠመቀ ለ፫ ዓመታት አስተማረ፣ ስለ ኃጢአታችን በመስቀል ላይ ቤዛ ሆነልን፡፡ በሦስተኛውም ቀን ከሙታንተለይቶ ተነሣ፤ ለደቀ መዛሙርቱም ተገለጠላቸው፡፡

ዛሬም ጌታችን ኢየሱስ ከዕርገቱ በፊት ከተነሣ በኋላ ስላስተማራቸው ትምህርቶች፣ ደቀመዛሙርቱን ስላዘዛቸው ትዕዛዝ እናያለን፡፡

ጌታችን ከተነሣ በኋላ ባሉት ፵ ቀናት በተለያዩ ጊዜያት ለደቀመዛሙርቱ ተገልጾ ስለ እግዚአብሔር መንግሥት ያስተምራቸው ነበር፡፡ ስለክርስቶስ የተነገረውን የቅዱሳት መጻሕፍት ትንቢት ከዚያ በፊት አላስተዋሉም ነበር፡፡ ጌታችንም ስለ እርሱ የተጻፉትን ተረጎመላቸው፣ አዕምሮቸውንም ከፈተላቸው መጻሕፍትንም አስተዋሉ፤ እምነታቸውን አጸናላቸው፡፡ ስለ ትንሣኤው የነበራቸውን ጥርጣሬም ከልቦናቸው አጸዳላቸው፡፡

የሚከተሉትን ትዕዛዛት እና ኃላፊነቶችም ሰጣቸው፡-
* ወደ ዓለም ሁሉ ሂዱ ወንጌልንም ለፍጥረት ሁሉ ስበኩ፡፡ ማር ፲፮ ፥ ፲፭

* ዮሐንስ በውኃ አጥምቆ ነበርና እናንተ ግን ከጥቂት ቀን በኋላ በመንፈስ ቅዱስ ትጠመቃላችሁ፡፡ የሐዋ ፩ ፥ ፭

* እንግዲህ ሂዱና አሕዛብን ሁሉ በአብ በወልድና በመንፈስ ቅዱስ ስም እያጠመቃችሁ… አስተምሯቸው፡፡ ማቴ. ፳፰ ፥ ፲፱ – ፳

* እስከ ምድር ዳርም ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ፡፡ የሐዋ.ሥ ፩ ፥ ፰

በወንጌል ለመስበክ እና በስሙ ለማጥመቅ ወደ ዓለም ሲወጡ፣ እንደሚገረፉ ወደ ነገሥታት የፍርድ አደባባይም እንደሚያወጧቸው ነገሯቸዋል፡፡ እስከመጨረሻም የጸና ግን ይድናል በማለትእስከ ዓለም ፍጻሜ ከእነርሱ ጋር እንደሚሆንና መንፈስ ቅዱስን ሲቀበሉ ኃይልን እንደ ሚያገኙምቃል ገብቶላቸዋል፡፡

ከሙታን በተነሣ በ፵ ኛው ቀን ደቀመዛሙርቱን ወደ ደብረዘይት ወሰዳቸውና ባረካቸው፡፡ ተሰብስበው ትምህርቱን እየሰሙም ወደ ሰማይ ከፍ ከፍ አለ፡፡ ወደ ሰማይም ዐረገ ደመናም ከዓይናቸው ሰወረው፡፡

ደቀመዛሙርቱ ክርስቶስ ወደ ዐረገበት ቀና ብለው እየተመለከቱ ሳለ ሁለት መላዕክት ነጫጭ ልብስ ለብሰው በአጠገባቸው ቆመው “ወደ ሰማይ እየተመለከታችሁ ስለምን ቆማችኋል? ይሄ ከናንተ ወደ ሰማይ የወጣው ኢየሱስ ወደ ሰማይ ሲሄድ እንዳያችሁት እንዲሁ ይመጣል አሏቸው፡፡ ክርስቶስ ሞትን አሸንፎ በተነሣ በአርባኛው ቀን በድል ዐረገ፡፡ ወደ ሰማይ እያረገ ሲሄድ እንዳዩት ደግሞ በዓለም ላይ ሊፈርድ ይመጣል፡፡ ማረጉን አምነን ዳግም መምጣቱን እንናፍቅ፡፡�

” ደቀመዛሙርቱም ጌታ ካረገበት ከደብረ ዘይት እግዚአብሔርን እያከበሩ ተመለሱ፡፡ እንደታዘዙት መንፈስ ቅዱስን እስኪቀበሉም በኢየሩሳሌም ቆዩ ፡፡

እኛም በኢየሩሳሌም በተመሰለች ቅድስት ቤተ ክርስቲያን በጸሎትና በአገልግሎት በመትጋት ልንቆይ ይገባል ።

ወስብሐት ለእግዚአብሔር

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on LinkedIn
  • Share on Telegram
  • Share by Mail
https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/ዕርገት.jpg 720 1280 gssu https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/logo-2-1-300x74-1.png gssu2023-05-25 07:58:392023-05-25 08:00:45ዕርገተ ክርስቶስ
Search Search

Recent Posts

  • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ
  • ሦስተኛ ዙር የ፲፪ ክፍል ምርቃት መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት ተከናወነ።

Archives

  • April 2026
  • September 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • May 2025
  • April 2025
  • October 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • July 2022
  • June 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
© Ethiopian Orthodox Church Global Sunday School Union | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
  • Link to Youtube
  • Link to Telegram
  • Link to TikTok
Link to: ቤተ ክርስትያን እና አመራሮቿ Link to: ቤተ ክርስትያን እና አመራሮቿ ቤተ ክርስትያን እና አመራሮቿ Link to: ፲፪ኛው የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ የአቋም መግለጫ Link to: ፲፪ኛው የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ የአቋም መግለጫ ፲፪ኛው የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top