የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት - በኢ/ኦ/ተ/ቤ የመንበረ ፓትርያርክ ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ አንድነቱ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ተቋማዊ ራእይ፣ ተልእኮ
      • መዋቅራዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቋማዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማስፈጸሚያ
    • ስልታዊ እቅድ 2018 – 2021 ዓ/ም
  • ሥርዓተ ትምህርት
    • መሠረታዊ መረጃዎች
    • የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት አደረጃጀት መመሪያ
    • የሥርዓተ ትምህርቱ መመማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
    • የሥርዓተ ትምህርቱ ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ /ካሌንደር
    • የመምህራን ሥልጠና እና መልእክቶች
    • መጻሕፍቱን ለማግኘት እና ተጨማሪ መረጃ
    • ልዩ ልዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች
  • ፕሮጀክቶች
  • መዝሙረ ማኅሌት
    • የመስከረም ወር መዝሙሮች
      • የዮሐንስ መዝሙር
      • የመስቀል መዝሙሮች
      • የብዙኃን ማርያም መዝሙር (መስከረም ፳፩ )
      • የዘመነ ጽጌ መዝሙር
    • የጥቅምት ወር መዝሙሮች
      • የአብርሃ ወአጽብሐ መዝሙር (ጥቅምት 4 ቀን)
    • የኅዳር ወር መዝሙሮች
      • የቅዱስ ሚካኤል መዝሙር (ኅዳር 12 ቀን)
    • የጥር ወር መዝሙሮች
      • የዘመነ ጥምቀት መዝሙር
      • የቃና ዘገሊላ መዝሙር (ጥር 12 ቀን)
    • የመጋቢት ወር መዝሙሮች
      • የወርኃ ጾም መዝሙሮች
      • የሆሣዕና መዝሙራት
      • የሰሙነ ሕማማት መዝሙሮች
  • ዜና
    • አጫጭር ዜናዎች
    • ዝርዝር ዜናዎች
    • ወቅታዊ መረጃዎች
    • ማስታወቂያ
      • የሰንበት ትምህርት ቤቶች መጻሕፍት እንግሊዝኛ ትርጉም ሥራ ተሳትፎ ጥሪ
  • ያግኙን
  • ቋንቋ
    • ትግርኛ
    • Afaanoromo
  • Menu Menu

መዝሙር 289 - ከላይኛው ሀገር

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/1.-ከላይኛው-ሀገር.mp3

ከላይኛው ሀገር ከሰማያት ወርዶ

ከድንግል ማርያም በሥጋ ተወልዶ

ድንግል ማርያም ሆይ ያስገኘሽው ፍሬ

ለሕዝቦች አርአያ ተጠመቀ ዛሬ

መለኮት ኃያሉ ተኝቶ በበረት

እጅ መንሻ አመጡለት ሦስት ነገሥታት

ድንግል ማርያም ሆይ ያስገኘሽው ፍሬ

ለሕዝቦች አርአያ ተጠመቀ ዛሬ

ሎሌ ወደ ጌታው ነው እንጂ የሚሄድ

ጌታ እንዴት ይመጣል አገልጋዩ ዘንድ

አዝ•••

አጠምቅ ነበረ ባንተ ስም ሕዝቡን

እንዴት ብዬ ላጥምቅ አንተን ጌታዬን

አጥምቀኝ እኔን እንዲህም እያልክ

ከሣቴ ብርሃን ወልዱ ለቡሩክ

አዝ•••

እንደዚህ እያለ ሲያጠምቅ በልብ

መንፈስ ቅዱስ መጣ በአምሳለ ርግብ

አብም መሰከረ በደመና ሳለ

የምወደው ልጄ ይኽ ነው እያለ

አዝ•••

ወደ ሀገራቸው ለመሄድ ሲነሱ

በሄሮድስ በኩል እንዳይመለሱ

መልአኩ ነግሯቸው እነሱም አምነው

በሌላ ጎዳና ገቡ አገራቸው

አዝ•••

ሰማይና ምድርን እንዳልደነገገ

ከሕፃናት ጋራ በገሊላ አደገ

ከግብፅ ሲመለስ ኖሮ በስደት

ናዝራዊ ለመባል ኖረ በናዝሬት

መዝሙር 290 - ከድንግል ተወልዶ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/2.-ከድግል-ተወልዶ.mp3

ከድንግል ተወልዶ እኛን ሊቀድስ (፪)

ተጠመቀ ኢየሱስ ባሕረ ዮርዳኖስ (፪)

መጥምቁ ዮሐንስ ምንኛ ታደለ

ከነቢያት ሁሉ ሥልጣኑ ከፍ አለ

አዝ•••

ትንቢቱን ሊፈፅም አስቦ ክርስቶስ

ተጠምቆ አዳነን በባሕረ ዮርዳኖስ

አዝ•••

ምሥጢረ ሥላሴ ታየ የዚያን ዕለታ

ምን ይከፈለዋል ለአምላክ ውለታ

አዝ•••

እመቤቴ ማርያም ምነኛ ታደልሽ

ከአዳም ልጆች ሁሉ አንቺ ተመረጥሽ

አዝ•••

ቸሩ አምላካችን መድኃኔ ዓለምን

ኑ እናመስግነው ባንድነት ሆነን

-መዝሙር 291 - ዮሐንስ አጥመቆ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/3.-ዮሐንስ-አጥመቆ.mp3

ዮሐንስ አጥመቆ ለኢየሱስ (፪)

በፈለገ ዮርዳኖስ በፈለገ ፈለገ ዮርዳኖስ (፪)

(ቅዱስ ያሬድ)

መዝሙር 292 - 293 - ሖረ ኢየሱስ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/4.-ሖረ-ኢየሱስ.mp3

ሖረ ኢየሱስ (፬)

እም ገሊላ (፫) ኀበ ዮሐንስ (፪)

(ቅዱስ ያሬድ)

ሄደ ኢየሱስ ሄደ ኢየሱስ (፪)

ከገሊላ ከገሊላ ከገሊላ ወደ ዮሐንስ (፪)

መዝሙር 294 - ሖረ ኢየሱስ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/5.-ሖረ-ኢየሱስ.mp3

ሖረ ኢየሱስ  ሖረ ኢየሱስ(፪)

እም ገሊላ ኀበ ዮሐንስ እምገሊላ ኀበ ዮሐንስ (፪)

(ቅዱስ ያሬድ)

መዝሙር 295 - መጽአ ቃል

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/6.-መጽአ-ቃል.mp3

መጽአ ቃል እምደመና ዘይብል ዘይብል (፪)

ዝንቱ ውእቱ ወልድየ ዘአፈቅር(፪)

(ቅዱስ ያሬድ)

(ትርጉም)

መጣ ቃል ከደመና እንዲህ የሚል (፪)

የምወደው የማፈቅረው ልጄ ይህ ነው (፪)

መዝሙር 296 - ኀዲጎ ተሥዓ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/7.-ኀዲጎ-ተሥዓ.mp3

ኀዲጎ ተሥዓ ወተሥዓተ ነገደ (፪)

ማእከለ ባሕር (፬) ቆመ ማእከለ ባሕር (፪)

(ቅዱስ ያሬድ)

መዝሙር 297 - ተጠምቀ ሰማያዊ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/8.-ተጠምቀ-ሰማያዊ.mp3

ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ (፪)

ተጠምቀ ሰማያዊ በእደ መሬታዊ (፪)

ተጠምቀ ሰማያዊ በእደ መሬታዊ (፪)

ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ

አምላክ ሆይ ሕዝቦችህ ዳኑ በልደትህ

አምላክ ሆይ ሕዝቦችህ ዳኑ በጥምቀትህ

ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ

መዝሙር 298 - ኀዲጎ ተሥዓ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/7.-ኀዲጎ-ተሥዓ.mp3

ኀዲጎ ተሥዓ ወተሥዓተ ነገደ (፪)

ማእከለ ባሕር ቆመ ማእከለ ባሕር (፪)

(ቅዱስ ያሬድ)

መዝሙር 299 - ወተመሰሉ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/10.-ወተመሰሉ.mp3

ወተመሰሉ ሰብአ ዓይን አባግዐ ላባ ወማይ (፪)

ለኀበ አባግዕ ዘዮም ዘዮም ወጥምቀት ዐባይ (፪)

(አርኬ፣ ዜማ በሊቃውንት)

መዝሙር 300 - ነድ ለማየ ባሕር

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/11.-ነድ-ለማየ-ባሕር.mp3

ነድ ለማየ ባሕር ከበቦ (፪)

ማየ ባሕር ኀበ የሐውር ጸበቦ (፪)

(ነግሥ ፣ ዜማ በሊቃውንት)

መዝሙር 301 - እሰይ እሰይ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/12.-እሰይ-እሰይ.mp3

(በመቀባበል)

እሰይ እሰይ ተወለደ

እሰይ እሰይ ተጠመቀ

ከሰማየ ሰማያት ወረደ

ከድንግል ማርያም ተወለደ

እርሱ ባይወለድ   እሰይ እሰይ

ቸሩ አምላካችን      >>     >>

እርሱ ባይጠመቅ   >>     >>

መድኃኒታችን        >>     >>

መች ትገኝ ነበረ     >>    >>

ገነት ርስታችን       >>    >>

አዝ•••

ብርሃነ ወጣላቸው እሰይ እሰይ

ለእውነት ወገኖች    >>    >>

በጨለማ ጉዞ         >>    >>

እንዲያ ሲሰለቹ       >>    >>

አዝ•••

እንደ ጠል ወረደ   አሰይ እሰይ

ከሰማይ ወደ እኛ    >>    >>

ወገኖቹን ሊያድን    >>    >>

ከክፉ ቁራኛ           >>    >>

አዝ•••

(በኅብረት)

እግዚአብሔር አብ ላከ እሰይ እሰይ

አንድያ ልጁን                >>    >>

እርሱ ወዷልና               >>     >>

እንዲሁ ዓለሙን            >>    >>

መዝሙር 302 - ዮሐንስኒ ሀሎ ያጠምቅ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/13.-ዮሐንስኒ-ሀሎ-ያጠምቅ.mp3

ዮሐንስኒ ሀሎ ያጠምቅ (፪)

በሄኖን በቁሩበ ሳሌም  (፪)

(ቅዱስ ያሬድ)

መዝሙር 303 - ወረደ ወልድ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/14.-ወረደ-ወልድ.mp3

ወረደ ወልድ (፮)

እም ሰማያት ውስተ ምጥማቃት (፬)

(ቅዱስ ያሬድ)

መዝሙር 304 - እንዘ ሕፃን

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/15.-እንዘ-ሕፃን.mp3

እንዘ ሕፃን ልሕቀ በዮርዳኖስ ተጠምቀ (፪)

በዮርዳኖስ (፬) ተጠምቀ በዮርዳኖስ (፪)

(ቅዱስ ያሬድ)

መዝሙር 305 - በፍሥሓ ወበሰላም

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/16.-በፍሥሓ-ወበሰላም.mp3

በፍሥሓ በፍሥሓ ወበሰላም (፪)

ወረደ ወልድ (፬) ወልድ ውስተ ምጥማቃት (፪)

(ቅዱስ ያሬድ)

መዝሙር 306 - ግነዩ ለእግዚአብሔር

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/17.-ግነዩ-ለእግዚአብሔር.mp3

(በኅብረት)

ግነዩ ለእግዚአብሔር እስመ ኄር(፪)

እስመ ለዓለም ምሕረቱ እስመ ለዓለም(፬)

እናመስግንሽ የአምላክ እናት በዝማሬ (፪)

የዓለም ቤዛ ነውና የማኀፀንሽ ፍሬ(፬)

ከሰማየ ሰማያት ወርዶ ካንቺ ተወልዶ(፪)

መለኮት ወረደ ዮርዳኖስ እኛን ለመቀደስ(፬)

በድንግልናሽ የወድሽው ክርስቶስ(፪)

የድኩማን ብርታት ነው የሕሙማን ፈውስ(፬)

በዮሐንስ እጅ ተጠመቀ ዕዳችንን ፋቀ(፪)

በቸርነቱ ጠብቆ ከበደል አራቀን (፬)

ስምሽን የጠራ ዝክርሽንም ያዘከረ(፪)

በመንግሥተ ሰማያት ይኖራል እንደተከበረ (፬)

ብርሃነ መለኮት ያደረብሽ አዳራሽ(፪)

ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ድንግል አንቺ ነሽ(፬)

እመቤታችን እናታችን ማርያም(፪)

የተማፀነሽ ይድናል ለዘለዓለም (፬)

ድንግልናሽም ሳይለወጥ ወልድን የወለድሽ (፪)

የጌታችን እናት ማርያም ድንግል አንቺ ነሽ(፬)

(ሢራክ ታደሰ)

መዝሙር 307 - በጎል በጎል

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/18.-በጎል-በጎል.mp3

(በመቀባበል)

በጎል በጎል ሰብአ ሰገል (፬)

በጎል ሰብአ ሰገል ሰገዱ ሎቱ (፬)

ፀሐይ (፫) ፀሐይ ሠረቀ (፬)

ፀሐይ ሠረቀ ክርስቶስ ተጠምቀ (፬)

አንቺ ዮርዳኖስ (፬) ምንኛ ታደልሽ (፬)

የእግዚአብሔር መንፈስ ከላይ ወርዶልሽ (፬)

የዓለም መድኃኒት ተጠመቀብሽ (፬)

ድንግል ማርያም (፬) ንጽሕት ቅድስት (፬)

የጌታ እናት ምሥጋና ይገባሻል (፬)

ከሴቶች ሁሉ አንቺ ተመርጠሻል (፬)

ዕልል ዕልል (፬) ደስ ይበለን (፬)

ወልድ ተወልዶ ነፃ አወጣን (፪)

ዮሐንስ ሲያጠምቀው ድል አገኘን (፪)

መዝሙር 308 - በእደ ዮሐንስ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/19.-በእደ-ዮሐንስ-ተጠምቀ.mp3

በእደ ዮሐንስ ተጠመቀ ኢየሱስ ናዝራዊ (፪)

ሰማያዊ (፭) ኢየሱስ ናዝራዊ (፪)

መዝሙር 309 - እግዚኡ መርሐ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/20.-እግዚኡ-መርሐ.mp3

እግዚኡ መርሐ ዮርዳኖስ አብጽሐ (፪)

ወበህየ ዮሐንስ ወበህየ ፍጹመ ተፈሥሐ (፪)

(ትርጉም)

ጌታውን መራና ከዮርዳኖስ አደረሰው (፪)

በዚህም ዮሐንስ (፪) በፍጹም  ደስ አለው (፪)

(ቅዱስ ያሬድ)

መዝሙር 310 - ውስተ ማኀፀነ ድንግል

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/21.-ውስተ-ማኀፀነ-ድንግል.mp3

ውስተ ማኀፀነ ድንግል ኀደረ ማኀፀነ ድንግል (፪)

ሰማይ ወምድር ዘኢያገምሮ (፪) በማይ ተጠምቀ (፪)

(ቅዱስ ያሬድ)

መዝሙር 311 - ክርስቶስ ተወልደ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/22.-ክርስቶስ-ተወልደ.mp3

ክርስቶስ ተወልደ ክርስቶስ ተጠምቀ ክርስቶስ ተወልደ (፪)

ወለደነ ዳግመ ወለደነ ዳግመ እመንፈስ ቅዱስ ወማይ (፪)

(ቅዱስ ያሬድ)

መዝሙር 312 - የዓለምን በደል

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/23.-የዓለምን-በደል.mp3

የዓለምን በደል የሰውን ግፍ አይቶ

ዘጠና ዘጠኙን መላእክትን ትቶ

ጽድቅን ለመፈጸም በደልን አጥፍቶ

የሰላሙ መሪ የሰላሙ ዳኛ

አምላክ ተወለደ ተጠመቀ ለኛ

የሰማዮች ሰማይ የማይችለው ንጉሥ

ተወልዶ ሲጠመቅ እኛን ለመቀደስ

ተራሮች ደንግጠው ዘለሉ እንደ ፈረስ

አዝ•••

ባሕር ተጨነቀች ጠበባት መሬቱ

ዮርዳኖስም ሸሸ አልቆመም ከፊቱ

እንደ ተናገረው ዳዊት በትንቢቱ

አዝ•••

ልጁ በዮርዳኖስ ጽድቅን ሲመሠርት

መጣ በደመና ሰማያዊው አባት

እየመሰከረ የልጁን ጌትነት

አዝ•••

እንደምናነበው በወንጌል ተጽፎ

መንፈሰ ቅዱስ ታየ በራሱ ላይ ዓርፎ

በርግብ ምሳሌ ክንፉን አሠይፎ

አዝ•••

ባሕር ስትጨነቅ ተራራው ሲዘምር

ሰማዩ ሲከፈት ደመናው ሲናገር

ዓለም በዛሬው ቀን አየች ታላቅ ምሥጢር

(መልአከ ታቦር ተሾመ ዘርይሁን )

መዝሙር 313 - አምላክ ከዮርዳኖስ

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/24.-አምላክ-ከዮርዳኖስ.mp3

አምላክ ከዮርዳኖስ (፪) ተጠምቆ ሲወጣ (፪)

ሰማያት ተከፍተው (፪) ከሰማይ ቃል መጣ

ቃሉም አንዲህ ነበር (፪) እንደሚከተለው (፪)

የምወደው ልጄ (፫) ይህ ነው የሚል ነው

ዘጠና ዘጠኙን (፪) መላዕክቱን ትቶ (፪)

አምላክ ተጠመቀ (፫) በዮርዳኖስ ገብቶ

ዕፁብ ድንቅ ነው (፪) ይገርማል በውኑ (፪)

ሰማያዊ አምላክ (፫) ምድራዊ መሆኑ

አብ የነገረለት (፪) በደመና ወርዶ (፪)

ተጠምቆ አዳነን (፫) ከድንግል ተወልዶ

(ብርሃኑ ውድነህ)

መዝሙር 314 - ጥምቀተ ባሕር

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/25.-ጥምቀተ-ባሕር.mp3

ጥምቀተ ባሕር ዮርዳኖስ ነያ (፪)

ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ

ጌታችን ሲጠመቅ ባሕር ምን አለች

አልችለውም ብላ ወደ  ኋላ ሸሸች

ብርሃነ መለኮት በወንዙ ሲመላ

ዮርዳኖስም ሸሸ ኼደ ወደ ኋላ

አዝ •••

አብ በመጣ ጊዜ ደመናውን ጭኖ

መንፈስ ቅዱስ ታየ በርግብ አምሳል ሆኖ

ለልጁ ምስክር ሊሆን ፈለገና

ቃሉን ተናገረ ሆኖ በደመና

አዝ•••

ጌታችን ሲጠመቅ በሠላሳ ዓመት

ባሕር ኮበለለች ግኡዟ ፍጥረት

ሰማይ ተከፈተ ሆነልን ፀዓዳ

ምሥጢረ ሥላሴ ታወቀ ተረዳ

አዝ•••

ዕዕልል በይ ዮርዳኖስ የጥምቀት መገኛ

የጽድቅ መሰላል የድኀነት መዋኛ

ቀላያተ አብርሕት ብዙዎቸ እያሉ

እንደምን ተመረጥሽ ዮርዳኖስ ከሁሉ

መዝሙር 315 - ነፃነት አገኘን

https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/26.-ነፃነት-አገኘነ.mp3

በዛሬው ጥምቀቱ ተነግሮ አዋጅ

ነፃነት አገኘን በእግዚአብሔር አብ ልጅ

እሰይ እሰይ ተወለደ (፪)

ከሰማየ ሰማያት ወረደ (፪)

በቅዱስ ዮሐንስ ተጠመቀ (፪)

አብ መሰከረለት በደመና ሳለ

የምወደው ልጄ ይኼ ነው እያለ

አዝ•••

ጌታ በዮሐንስ ሊጠመቅ ሲል ገና

ወደ ኋላ ሸሸ ዮርዳኖስ ፈራና

አዝ•••

እንደ አንበሳ ደቦል ተራሮች ዘለሉ

ዕፁብ ነው ድንቅ ነው ግሩም ነው እያሉ

(መዝሙረ ስብሐት)

ለሌሎች ያጋሩ
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on LinkedIn
  • Share on Telegram
  • Share by Mail
Search Search

Recent Posts

  • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ
  • ሦስተኛ ዙር የ፲፪ ክፍል ምርቃት መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት ተከናወነ።

Archives

  • April 2026
  • September 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • May 2025
  • April 2025
  • October 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • July 2022
  • June 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
© Ethiopian Orthodox Church Global Sunday School Union | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
  • Link to Youtube
  • Link to Telegram
  • Link to TikTok
Link to: የቅዱስ ሚካኤል መዝሙር (ኅዳር 12 ቀን) Link to: የቅዱስ ሚካኤል መዝሙር (ኅዳር 12 ቀን) የቅዱስ ሚካኤል መዝሙር (ኅዳር 12 ቀን) Link to: የቃና ዘገሊላ መዝሙር (ጥር 12 ቀን) Link to: የቃና ዘገሊላ መዝሙር (ጥር 12 ቀን) የቃና ዘገሊላ መዝሙር (ጥር 12 ቀን)
Scroll to top Scroll to top Scroll to top