የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት - በኢ/ኦ/ተ/ቤ የመንበረ ፓትርያርክ ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ አንድነቱ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ተቋማዊ ራእይ፣ ተልእኮ
      • መዋቅራዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቋማዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማስፈጸሚያ
    • ስልታዊ እቅድ 2018 – 2021 ዓ/ም
  • ሥርዓተ ትምህርት
    • መሠረታዊ መረጃዎች
    • የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት አደረጃጀት መመሪያ
    • የሥርዓተ ትምህርቱ መመማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
    • የሥርዓተ ትምህርቱ ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ /ካሌንደር
    • የመምህራን ሥልጠና እና መልእክቶች
    • መጻሕፍቱን ለማግኘት እና ተጨማሪ መረጃ
    • ልዩ ልዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች
  • ፕሮጀክቶች
  • መዝሙረ ማኅሌት
    • የመስከረም ወር መዝሙሮች
      • የዮሐንስ መዝሙር
      • የመስቀል መዝሙሮች
      • የብዙኃን ማርያም መዝሙር (መስከረም ፳፩ )
      • የዘመነ ጽጌ መዝሙር
    • የጥቅምት ወር መዝሙሮች
      • የአብርሃ ወአጽብሐ መዝሙር (ጥቅምት 4 ቀን)
    • የኅዳር ወር መዝሙሮች
      • የቅዱስ ሚካኤል መዝሙር (ኅዳር 12 ቀን)
    • የጥር ወር መዝሙሮች
      • የዘመነ ጥምቀት መዝሙር
      • የቃና ዘገሊላ መዝሙር (ጥር 12 ቀን)
    • የመጋቢት ወር መዝሙሮች
      • የወርኃ ጾም መዝሙሮች
      • የሆሣዕና መዝሙራት
      • የሰሙነ ሕማማት መዝሙሮች
  • ዜና
    • አጫጭር ዜናዎች
    • ዝርዝር ዜናዎች
    • ወቅታዊ መረጃዎች
    • ማስታወቂያ
      • የሰንበት ትምህርት ቤቶች መጻሕፍት እንግሊዝኛ ትርጉም ሥራ ተሳትፎ ጥሪ
  • ያግኙን
  • ቋንቋ
    • ትግርኛ
    • Afaanoromo
  • Menu Menu

የዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ዮናታን እስር

የዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ዮናታን እስር

የዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ዮናታን እስር

ሊቀ ጳጳስ ዮናታን በዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የተልኪና ብራስላቭ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ናቸው። የሀገሪቱ መንግሥት ዩክሬን የምትመራበትን ወንጀለኛ መቅጫ ሕግ አንቀጽ 109፣ 110፣ 161 እና 436 (2) በመጥቀስ በአራት ወንጀሎች ጠርጥሬያቸዋለሁ በማለት ክስ ይመሠርትባቸዋል። ጉዳዩን በአግባቡ ለመረዳት ሊቀ ጳጳሱ የተከሰሱባቸው የወንጀል ሕጉ ድንጋጌዎች ምን ምን እንደሚሉ አስቀድመን እንመለከታለን።

  • አንቀጽ 109 በዐመጽ ለውጥ ለማምጣት ወይም ሕገ መንግሥታዊ ሥርዓቱን ለማስወገድ ወይም በኃይል ሥልጣን ለመያዝ የሚፈጸሙ ተግባራት
  • አንቀጽ 110 – የዩክሬንን ሉዓላዊ የግዛት ወሰን ማለፍ ወይም ዳር ድንበሯን ለመለወጥ አስቦ መሥራት
  • አንቀጽ 161 – ዘርን፣ ሃይማኖትን እና ዜግነትን መሠረት በማድረግ ልዩነት መፍጠር
  • አንቀጽ 463 (2) – የጦርነት ፕሮፖጋንዳ መንዛት (ሩሲያ በዩክሬን ላይ የፈጸመችውን የኃይል ወረራ አይቀበሉም፣ ለሕጋዊነቱ ዕውቅና ሰጥተዋል፤ የሩሲያ ወታደሮችን አድንቀዋል) የሚሉ ናቸው።

ለክሱ መነሻ የሆነው በራሪ ወረቀቶችን በማሰራጨት የዐመጽ ጥሪ አድርገዋል የሚል ነው። ነገር ግን ለአስረጅነት የቀረቡት በራሪ ወረቀቶች በማንና መቼ እንደ ተዘጋጁ ዐቃቤ ሕግ በማስረጃ ያረጋገጠው ነገር የለም። ይህም ሆኖ ግን የቪኒሺያ ከተማ ፍርድ ቤት ነሐሴ 1 ቀን 2015 ዓ.ም ሊቀ ጳጳስ ዮናታን የአምስት ዐመት እስር እንዲፈጸምባቸው እና ንብረታቸው እንዲወረስ ውሳኔ አስተላልፏል።

ከውሳኔው በኋላ የዩክሬን ቤተ ክርስቲያን ሕግ መምሪያ የሊቀ ጳጳሱ መታሰር የዩክሬን ሕገ መንግሥት፣ የወንጀል ሕጉን እና ሥነ ሥርዓት በመጣስ የተፈጸመ መሆኑን ገልጿል። ስለ ሕገ ወጥነቱም ሲያብራራ ብዙ መረጃዎች የወንጀል ሕግ ሥነ ሥርዓቱን ባልተከተለ መንገድ እንደተካተቱ ይህም ከዩክሬን የወንጀል ሕግ ሥነ ሥርዓት አንቀጽ 291 እና ከዩክሬን ሕገ መንግሥት አንቀጽ 62 ጋር የሚቃረን መሆኑን ገልጿል። ዐቃቤ ሕግ በሌለው ሥልጣን በመጥሪያ ወረቀቱ ላይ መፈረሙ፣ ሊቀ ጳጳሱን እንደ መንግሥት ባለሥልጣን መቁጠሩ፣ ዐቃቤ ሕግ ሙከራ አድርገዋል ካለ በኋላ ወንጀሉን እንደፈጸሙ አድርጎ ክስ ማቅረቡ እርስ በርሱ የሚጣረስ መሆኑ፣ ለክሱ መነሻ የሆኑት በራሪ ወረቀቶች ቤታቸው በተበረበረበት ወቅት የተገኙ ናቸው ተብለው ቢቀርቡም በወቅቱ ስለመገኘታቸው መርማሪዎቹም ሆኑ ምስክሮች ያላስረዱና በቀረጻውም ወቅት ያልታዩ መሆናቸው፣ መቼና በማን የተዘጋጁ እንደሆነ ባልተረጋገጡ ወረቀቶች ላይ መመሥረቱ እና ያለ ምንም ማስረጃ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 161 መጥቀሱ ሌሎች የክሱን ሒደት አግባብነት የሌለው የሚያደርጉ ማሳያዎች መሆናቸውን ይጠቅሳል።

የዩክሬን መንግሥት ከየካቲት 2014 ዓ.ም ጀምሮ በዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ካህናት ላይ 65 ክሶች መሥርቷል። 19 ካህናት ደግሞ የዩክሬን ዜግነታቸውን ተነጥቀዋል። ከእነዚህም መካከል ሊቀ ጳጳስ ዮናታን አንዱ ናቸው። ሊቀ ጳጳሱ በትውልድ የዩክሬን፣ የሩሲያና የቤላሩስ ዝርያ ያላቸው ሲሆን ከ1991 ዓ.ም (እ.ኤ.አ) ጀምሮ የዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ከሩሲያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን መለየት የለባትም በሚል አሳብ አቅርበው ነበር። በዚህም ምክንያቱ በወቅቱ የኬቭና መላው ዩክሬን ሊቀ ጳጳስ ከነበሩት ፊላሬት (በአሁኑ ሰዓት ከሩሲያ የተገነጠለው የዩክሬን ቤተ ክርስቲያን መሪ) ጋር በመጋጨታቸው ከአገልግሎት ታግደው ቆይተዋል። በ1992 ዓ.ም ሊቀ ጳጳስ ፊላሬት ተወግዘው በምትካቸው ሊቀ ጳጳስ ቭላድሚር የኬቭና መላው ዩክሬን ሊቀ ጳጳስ ሆነው ሲሾሙ እገዳቸው ቀኖናዊ እና ሕጋዊ ሆኖ ስላልተገኘ ተሽሯል።

ከ2022 ጀምሮ እየተካሄደ በሚገኘው የዩክሬን እና ሩሲያ ጦርነት ሊቀ ጳጳስ ዮናታን ቀድሞ በነበራቸው አቋም ብዙ ግፎች ሲፈጸምባቸው ቆይቷል። ሊቀ ጳጳሱ የ74 ዐመት አዛውንት ከመሆናቸውም በላይ በተደጋጋሚ የቀዶ ጥገና ሕክምና የተደረጉላቸው የኢንሱሊን ተጠቃሚ ናቸው። ዜግነታቸውን በመነጠቃቸው ምክንያት የጤና መድኅን መብት እና ሕጋዊ ከለላ ተነፍጓቸዋል። ዜግነታቸው እንዲነጠቅ የተደረገው በዩክሬኑ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ዜለንስኪ ቀትተኛ ትእዛዝ ነው። ስለሆነም ክሳቸው የሕግ መተላለፍን መሠረት ያደረገ ሳይሆን ፖለቲካዊ ጫና ያጠላበት መሆኑን መረዳት ይገባል። ይህም በዐለም አቀፍ ደረጃ ኦርቶዶክሳውያን ላይ የተከፈተው ጥቃት አንዱ ማሳያ ሆኖ ሊቀርብ የሚችል ነው። በእኛ ሀገር በኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚፈጸመውም የዚህ ተመሳሳይ ነው።

የሊቀ ጳጳሱን እስር ተከትሎ በጉዳዩ መልእክት ያስተላለፉት የሩሲያው ፓትርያርክ ቄርሎስ “በሊቀ ጳጳስ ዮናታን ላይ የተላለፈው እስር ሊቀ ጳጳሱ ለቤተ ክርስቲያን እና ለክርስቶስ ታማኝ በመሆናቸው ጫና ውስጥ ለመክተት ታስቦ የተደረገ ነው” ብለዋል። አክለውም ሊቀ ጳጳስ ዮናታን እንደ ማንኛውም የቤተ ክርስቲያን አባት ስለ ሰላም የሚጸልዩ፣ የሩሲያን መንፈሳዊ  አንድነት የሚናፍቁ፣ መከፋፈልን የሚጸየፉ እና የዩክሬንን ቤተ ክርስቲያን ጥቅምና መብት ለማስከበር የሚተጉ ናቸው” ብለዋል። ከዚህ የምንረዳው በፖለቲካ ግፊት የዩክሬንን ቤተ ክርስቲያን ከሩሲያ ቤተ ክርስቲያን ለመገንጠል በሚደረገው ሒደት ሊቀ ጳጳሱ ዮናታን “እንቅፋት” ሆነው የተገኙ መሆናቸውን ነው። ሊቀ ጳጳሱ በአገልግሎታቸውና በመንፈሳዊ አባትነታቸው በመልካም አርአያነት የሚጠቀሱ ቢሆንም ያለ በቂ ምክንያት ለእስር መዳረጋቸው ዓለም የጸና እምነት ያላቸውን ኦርቶዶክሳውያን እያሳደደች ለመሆኑ አንድ ማሳያ ነው።

 

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on LinkedIn
  • Share on Telegram
  • Share by Mail
https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/ሊቀ-ጳጳስ.jpg 1080 1920 Abenezer Mamushet https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/logo-2-1-300x74-1.png Abenezer Mamushet2023-10-11 21:39:232023-10-11 21:39:23የዩክሬን ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ዮናታን እስር
Search Search

Recent Posts

  • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ
  • ሦስተኛ ዙር የ፲፪ ክፍል ምርቃት መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት ተከናወነ።

Archives

  • April 2026
  • September 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • May 2025
  • April 2025
  • October 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • July 2022
  • June 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
© Ethiopian Orthodox Church Global Sunday School Union | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
  • Link to Youtube
  • Link to Telegram
  • Link to TikTok
Link to: “ክርስቲያኖች መተት አደረጉብን” Link to: “ክርስቲያኖች መተት አደረጉብን” “ክርስቲያኖች መተት አደረጉብን” Link to: የነገረ ሰብእ ትምህርት ጉድለት የወለደው አገራዊ ቀውስ Link to: የነገረ ሰብእ ትምህርት ጉድለት የወለደው አገራዊ ቀውስ የነገረ ሰብእ ትምህርት ጉድለት የወለደው አገራዊ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top