የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት - በኢ/ኦ/ተ/ቤ የመንበረ ፓትርያርክ ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ አንድነቱ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ተቋማዊ ራእይ፣ ተልእኮ
      • መዋቅራዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቋማዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማስፈጸሚያ
    • ስልታዊ እቅድ 2018 – 2021 ዓ/ም
  • ሥርዓተ ትምህርት
    • መሠረታዊ መረጃዎች
    • የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት አደረጃጀት መመሪያ
    • የሥርዓተ ትምህርቱ መመማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
    • የሥርዓተ ትምህርቱ ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ /ካሌንደር
    • የመምህራን ሥልጠና እና መልእክቶች
    • መጻሕፍቱን ለማግኘት እና ተጨማሪ መረጃ
    • ልዩ ልዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች
  • ፕሮጀክቶች
  • መዝሙረ ማኅሌት
    • የመስከረም ወር መዝሙሮች
      • የዮሐንስ መዝሙር
      • የመስቀል መዝሙሮች
      • የብዙኃን ማርያም መዝሙር (መስከረም ፳፩ )
      • የዘመነ ጽጌ መዝሙር
    • የጥቅምት ወር መዝሙሮች
      • የአብርሃ ወአጽብሐ መዝሙር (ጥቅምት 4 ቀን)
    • የኅዳር ወር መዝሙሮች
      • የቅዱስ ሚካኤል መዝሙር (ኅዳር 12 ቀን)
    • የጥር ወር መዝሙሮች
      • የዘመነ ጥምቀት መዝሙር
      • የቃና ዘገሊላ መዝሙር (ጥር 12 ቀን)
    • የመጋቢት ወር መዝሙሮች
      • የወርኃ ጾም መዝሙሮች
      • የሆሣዕና መዝሙራት
      • የሰሙነ ሕማማት መዝሙሮች
  • ዜና
    • አጫጭር ዜናዎች
    • ዝርዝር ዜናዎች
    • ወቅታዊ መረጃዎች
    • ማስታወቂያ
      • የሰንበት ትምህርት ቤቶች መጻሕፍት እንግሊዝኛ ትርጉም ሥራ ተሳትፎ ጥሪ
  • ያግኙን
  • ቋንቋ
    • ትግርኛ
    • Afaanoromo
  • Menu Menu

ለአገራችን ኢትዮጵያ ሰላምን ስጣት

ለአገራችን ኢትዮጵያ ሰላምን ስጣት

ለአገራችን ኢትዮጵያ ሰላምን ስጣት

ሊቀ ነቢያት ሙሴ እስራኤላውያን ከአሕዛብ ነገሥታት ጋር ጦርነት በሚያደርጉበት ወቅት ወንድሞቻችሁ ወደ ጦርነት ሔደው እናንተ ከቤታችሁ ተቀምጣችኋል ሲላቸው “እኛ ባሪያዎችህ ሁላችን ጋሻ ጦራችንን ይዘን በእግዚአብሔር ፊት ጌታችን እንደተናገረ ወደ ጦርነት እንሔዳለን” (ዘኁ. ፴፪፡፳፯) የሚል መልስ ሰጥተውታል። በዓለም ላይ ሰላም ሲታጣ  አገራት ሰላም አስከባሪ ኃይል በመላክ ሰላምን በፈረስ አንገት፣ በጦር አንደበት ሊያመጧት ይሻሉ። የተከሠተውን የሰላም እጦት ወደ ነበረበት ለመመለስ ጦርነት ያውጃሉ። ሰላምን የሚሹ ሁሉ ለጦርነት እንዲዘጋጁ ዐዋጅ ይነግራሉ። ሰላም የጦርነት አለመኖር ቢሆንም የሚለካው በውጤቱ ነውና የተባለው ሰላም እስከሚመጣ ሕዝቡ በጦርነት ይሳተፋል። ይህ የዕለት ከዕለት የየአገራት አነዋወር መገለጫ ነው።

ምክንያታቸው ምንም ቢሆን ጦርነቶች የሚካሔዱት የጋራ ትውውቅ እንኳን በሌላቸው አካላት መካከል የመሆን ዕድላቸው ሰፊ ነው። ዣን ዥሮዱ የተባለ ፈረንሳያዊ ደራሲ እንደ ተናገረው በአብዛኛው ጦርነት እርስ በርሳቸው በሚተዋወቁና በሚጠላሉ ሰዎች ውሳኔ ለመጠላላት ቀርቶ ለመተዋወቅ እንኳ ዕድል በሌላቸው ሰዎች መካከል የሚደረግ ነው። በጦርነቱ ሒደት በውጊያው ዐውድ ላይ የሚገኙት የጦርነትን አስከፊነት ስለሚያውቁት ጦርነትን ይጸየፉታል፤ ይጠሉታል። ከዐውደ ውጊያው ርቀው ያሉት የጦርነቱ ዘዋሪዎች ደግሞ ሞት ከደጃቸው እንደሚደረስ በመዘንጋት የጦርነቱን መግፋት ይፈልጉታል። ጦርነቱ በአንደኛው አሸናፊነት ካልተጠናቀቀ ደግሞ ‘ወታደሩ ያልቃል፤ መሪ ይታረቃል’ በሚለው ብሂል ከጦርነት በፊት ሊሔድባቸው ይገባል ተብለው በዐዋቂዎች የተነገሩ የዕርቅና የሰላም መንገዶች አማራጭ ተደርገው ሲወሰዱ ይታያል።

ጦርነት አስከፊ ነው። የሚጎዳው በጦርነት የተሰለፉ ወታደሮችን ብቻ ሳይሆን ሕፃናትን እና አዛውንቶችን ጭምር ነው። ጦርነት አማራጭ የሌለው መፍትሔ ነው። አገር ሊያፈርስ፣ ሃይማኖት ሊያረክስ ከመጣ ጠላት ጋር እንጂ ከማንም ጋር ጦርነት ሊኖር አይገባም ነበር። ይህም ሆኖ ሰው ራሱን የመከላከል ተፈጥሯዊና ሕጋዊ መብት ስላለው አንድ ሰው፣ ማኅበረሰብ፣ ሕዝብ ወይም አገር የተከፈተበትን ጦርነት ለመመከት ወደ ጦርነት ሊገባ ይችላል። ወደ ጦርነት ከመግባት በፊት ግን ሁሉንም የሰላም በሮች ሁሉ ማየት ይገባዋል። ጦርነትን እንደ አንድ የሥራ ዕቅድ መያዝ ተገቢ አይሆንም። የሰብአዊ መብት ተቋማት፣ ብሔራዊና ዓለም አቀፍ የሰላምና ደኅንት ተቋማትም ሰላምን ለማስከበር ኃላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል።

በተለይም ዓለም ከሚሰጠው ሰላም የተለየው ሰላም ለሰው ልጆች ሁሉ የምታድለው ቤተ ክርስቲያን ሰላምን በእጅጉ ልትሰብክና ወደ ጦርነት የሚገቡ አካላትን ከጦርነት ባሻገር ያሉ መፍትሔዎችን እንዲያማትሩ ልትመክር ይገባታል። ይህን የሰላም መንገድ እውን ማድረግ ግን ቀላል ተግባር አይደለም። መታመን፣ መከበርና መፈራት ይጠይቃል። ጌታችን አምላካችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስም “ሰላምን እተውላችኋለሁ፤ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ። እኔ የምሰጣችሁ ሰላም ዓለም እንደሚሰጣችሁ አይደለም” (ዮሐ. ፲፬፡፳፯) ብሎ የቤተ ክርስቲያን ሰላም ከዓለሙ ሰላም የተለየ መሆኑን ነግሮናል። ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ይህን ሰላም የገለጠው “አእምሮን ሁሉ የሚያልፍ፣ ልባችንን እና አሳባችንን የሚጠብቅ የእግዚአብሔር ሰላም” በማለት ነው (ፊል. ፩፡፪)። እንዲህ ዐይነቱ ሰላም በቀላሉ አይገኝም። ፈተናውም ከባድ ነው። የዓለሙ ሰላም ግን እግዚአብሔር በኤርምያስ አድሮ “የሕዝቤን ስብራት በጥቂቱ ይፈውሳሉ፤ ሰላም ሳይሆን፣ ሰላም ሰላም ይላሉ” (ኤር. ፮፡፲፬) በማለት የተናገረው ዐይነት ነው።

“ሰላምን የሚፈልግ ለጦርነት ይሰናዳ” እንደሚለው የዓለሙ ብሂል “በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ” (ኤፌ. ፬፡፫) የተባሉ ክርስቲያኖች በተለይም የቤተ ክርስቲያን አባቶች ሰላም ይመጣ ዘንድ ከሥጋዊ ፍላጎታቸውና መሻታቸው ጋር ጦርነት ሊገጥሙ፣ ሊያሸንፉና ለዓለሙ የሚተርፍ ሰላምን ሊሰብኩ ይገባል። ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ኢሳያስ “የምሥራች የሚናገር፣ ሰላምንም የሚያወራ፣ የመልካምንም ወሬ የምሥራች የሚናገር፣ መድኀኒትንም የሚያወራ፣ ጽዮንንም አምላክሽ ነግሦአል የሚል እግሩ በተራሮች ላይ እጅግ ያማረ ነው (ኢሳ. ፶፭፡፲፪) በማለት የሰላም መልእክተኞችን መልካምነት ነግሮናል።

የቤተ ክርስቲያን አባቶች የቤተ ክርስቲያን ዓላማና ግብ የሆነውን ለሰው ልጆች ሁሉ ሰላም የመስጠት ተልእኮ በአግባቡ ቢወጡ በዓለም ላይ የምናያቸው ችግሮች ሁሉ ይቃለሉ፤ ምናልባትም ይጠፉ ነበር። ይህን ሥራ ለመሥራት ብቁ የሚሆኑት ግን የራሳቸውን ጦርነት ማሸነፍ የቻሉት ብቻ ናቸው። ከሥጋዊና ደማዊ ትግል ወጥተው በሰማይ ቦታ ካላቸው ርኵሳን መናፍስት ጋር የሚያዋጉ ብሎም የሚያሸንፉ መሆን አለባቸው። ዓለምን የናቁ እንጂ በዓለሙ የተሸነፉ መሆን የለባቸውም። እነዚህ የተናገሩት ብቻ ሳይሆን ዝምታቸው ይሰማላቸዋል። ስለሆነም ቤተ ክርስቲያን በነበራት ክብርና ተሰሚነት ልክ ሰላም የማምጣት፣ ዕርቅ የማውረድ፣ መስተጻርራንን የማስታረቅና አገራዊ ሰላምን የማስከበር ዙፋን ላይ የማስቀመጥ ኃላፊነት በአባቶቻችን እጅ ላይ ነው። የሚናገሩትን የሚኖሩ፣ የማይኖሩትን የማይናገሩ፣ የሚፈሩና የሚከበሩ፣ በሕዝብ የሚታመኑና ለአገር ሰላም የሚለምኑ አባቶችን ፈልጎ ማግኘት የሚያሻበት አጣብቂኝ ጊዜ ላይ መሆናችን ሊታወቅ ይገባል። እንዲህ ዐይነት የአገር ዋርካዎች በሌሉን መጠን የኀጢአተኞችን ሰላም በማየት በዓመጸኞች ድርጊት በመቅናት ሰላምን በመግፋት፣ ሽማግሌዎችንም በመጥላት የሚኖሩት ጥቂት አይሆኑም።

የምንንኖርበት ዓለም ብርቱ ሰልፍ የሚካሔድበት መሆኑን በሕይወቱም፣ በትምህርቱም የነገረን ትዕግሥተኛው ኢዮብ “አንድ ሰው በሰላም ተዘልሎ ሲቀመጥ በሙሉ ኃይሉ ሳለ ይሞታል” (ኢዮ. ፳፩፡፳፫) ይለናል። ገዳይ ጦርነት ብቻ ሳይሆን የሚገድል ሰላምም እንዳለ ከዚህ ቃል መረዳት እንችላለን። ለዓለሙ መድኀኒት እንዲሆኑ በመንፈስ ቅዱስ የተመረጡ አባቶች ለመድኀኒትነት የሚያበቃቸውን ግብር ገንዘብ ለማድረግ የራሳቸውን ጦርነት በድል ካልተወጡ ሞት ነው። ለሕዝቦች ሰላምና አንድነት ካልጸለዩ፣ ጦርነት የሚጎስሙትን ካልገሠጹ፣ እምቢተኞችን ካላወገዙ፣ እንደ ሰማዕተ ጽድቅ ቅዱስ ጴጥሮስ ለእውነትና በእውነት ለመንጋዎቻቸው ካልቆሙ ሞት ነው።

ስለሆነም የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮዋና ስብከቷ ሁሉ “ከክፉ ሽሽ መልካምን አድርግ፤ ሰላምን እሻ፤ ተከተላትም” (መዝ. ፴፬፡፲፬) የሚል ነውና በአገራችን ሰላም እንዲመጣ ቤተ ክርስቲያን የራሷን ድርሻ ልትወጣ ይገባል። ሐዋርያው ያዕቆብም “የጽድቅም ፍሬ ሰላምን ለሚደርጉት ሰዎች በሰላም ይዘራል” (ያዕ. ፫፡፲፰) እንዳለ የሰላም ዘር መዝራት ይገባል። ይህን ማድረግ ባልተቻለ መጠን “ሰላምን በተስፋ ተጠባበቅን፣ መልካምም አልተገኘም’ የሚሉት ብዙ ይሆናሉ። ከእግዚአብሔር ጽኑ ቁጣ የተነሣም የሰላም በረት ይፈርሳልና ከቁጣው እንዲመለስልን ከማሳሰብ ጋር “ምሕረትና እውነት ተገናኙ፣ ጽድቅና ሰላም ተስማሙ” (መዝ. ፹፭፡፲) የምንልበት ጊዜ እንዲቀርብ መሥራት ጊዜ ሊሰጠው የማይገባ ጉዳይ ነው። ሰላም እንዲመጣ መሥራት እና ማስታረቅ እግዚአብሔር ለወዳጆቹ የሰጠው ሥልጣን ነው። “የሚያስታርቁ ብፁዓን ናቸው፤ የእግዚአብሔር ልጆች ይባላሉና” (ማቴ. ፭፡፲)። በተለይም የቤተ ክርስቲያን አባቶች የማስታረቅ ሥልጣናቸው ሰውን ከሰው ብቻ ሳይሆን ሰውን ከራሱ እና ከእግዚአብሔር ጭምር ነው። ስለሆነም ይህን ሥልጣን በማቃለል፣ በተንኮልና በሴራ እርቅ የሚያደርጉ በራሳቸው ላይ የእሳት ክምር ይጨምራሉና ሊጠነቀቁ ይገባል። አባቶችም ይህን ኃላፊነታቸውን ሲወጡ እግዚአብሔር በሰጣቸው ጥበብ “ሲታጠቡ ከክንድ፣ ሲታረቁ ከሆድ” የሚለውን ብሒል የተከተለ መሆኑን መመርመር አለባቸው። “በዘመኑ ፍጹም ሰላምን እግዚአብሔር ይሰጣት ዘንድ እግዚአብሔርን ስለምትወድ ስለ አገራችን ኢትዮጵያ እንማልዳለን” (በእንተ ቅድሳት)።

መልካም በዓል

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on LinkedIn
  • Share on Telegram
  • Share by Mail
https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/selam.jpg 1080 1920 Abenezer Mamushet https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/logo-2-1-300x74-1.png Abenezer Mamushet2023-09-12 22:22:352023-09-12 22:22:35ለአገራችን ኢትዮጵያ ሰላምን ስጣት
Search Search

Recent Posts

  • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ
  • ሦስተኛ ዙር የ፲፪ ክፍል ምርቃት መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት ተከናወነ።

Archives

  • April 2026
  • September 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • May 2025
  • April 2025
  • October 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • July 2022
  • June 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
© Ethiopian Orthodox Church Global Sunday School Union | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
  • Link to Youtube
  • Link to Telegram
  • Link to TikTok
Link to: ጦርነቱን ወደ ሰላም በማሸጋገር ምድሪቱንም፣ ትውልዱንም ማሳረፍ ከሁሉም ወገን ይጠበቃል Link to: ጦርነቱን ወደ ሰላም በማሸጋገር ምድሪቱንም፣ ትውልዱንም ማሳረፍ ከሁሉም ወገን ይጠበቃል ጦርነቱን ወደ ሰላም በማሸጋገር ምድሪቱንም፣ ትውልዱንም... Link to: የትግራይ ቤተ ክህነት እንቅስቃሴ ለተሐድሶ መናፍቃን ሰርግና ምላሽ Link to: የትግራይ ቤተ ክህነት እንቅስቃሴ ለተሐድሶ መናፍቃን ሰርግና ምላሽ የትግራይ ቤተ ክህነት እንቅስቃሴ ለተሐድሶ መናፍቃን...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top