የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት - በኢ/ኦ/ተ/ቤ የመንበረ ፓትርያርክ ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ አንድነቱ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ተቋማዊ ራእይ፣ ተልእኮ
      • መዋቅራዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቋማዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማስፈጸሚያ
    • ስልታዊ እቅድ 2018 – 2021 ዓ/ም
  • ሥርዓተ ትምህርት
    • መሠረታዊ መረጃዎች
    • የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት አደረጃጀት መመሪያ
    • የሥርዓተ ትምህርቱ መመማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
    • የሥርዓተ ትምህርቱ ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ /ካሌንደር
    • የመምህራን ሥልጠና እና መልእክቶች
    • መጻሕፍቱን ለማግኘት እና ተጨማሪ መረጃ
    • ልዩ ልዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች
  • ፕሮጀክቶች
  • መዝሙረ ማኅሌት
    • የመስከረም ወር መዝሙሮች
      • የዮሐንስ መዝሙር
      • የመስቀል መዝሙሮች
      • የብዙኃን ማርያም መዝሙር (መስከረም ፳፩ )
      • የዘመነ ጽጌ መዝሙር
    • የጥቅምት ወር መዝሙሮች
      • የአብርሃ ወአጽብሐ መዝሙር (ጥቅምት 4 ቀን)
    • የኅዳር ወር መዝሙሮች
      • የቅዱስ ሚካኤል መዝሙር (ኅዳር 12 ቀን)
    • የጥር ወር መዝሙሮች
      • የዘመነ ጥምቀት መዝሙር
      • የቃና ዘገሊላ መዝሙር (ጥር 12 ቀን)
    • የመጋቢት ወር መዝሙሮች
      • የወርኃ ጾም መዝሙሮች
      • የሆሣዕና መዝሙራት
      • የሰሙነ ሕማማት መዝሙሮች
  • ዜና
    • አጫጭር ዜናዎች
    • ዝርዝር ዜናዎች
    • ወቅታዊ መረጃዎች
    • ማስታወቂያ
      • የሰንበት ትምህርት ቤቶች መጻሕፍት እንግሊዝኛ ትርጉም ሥራ ተሳትፎ ጥሪ
  • ያግኙን
  • ቋንቋ
    • ትግርኛ
    • Afaanoromo
  • Menu Menu

“ኢሀሎ ዝየ ዳእሙ ተንሥአ በከመ ይቤ – ከዚህ የለም እንደ ተናገረው ተነሥቷል፡፡” ማቴ.28፡6

በጌታችን በመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መቃብር በራስጌና በግርጌ የነበሩ ቅዱሳን መላእክት ማልደው ወደ ጌታ መቃብር ለሄዱ ሴቶች ሕያውን ከሙታን መካከል ስለምን ትፈልጋላችሁ ከዚህ የለም እንደ ተናገረው ተነሥቷል በማለት መልሰውላቸዋል፡፡ ሴቶቹ ወደ መቃብሩ መሄድ የጌታችንን ሥጋ ሽቱ ለመቀባት ነበር፡፡ ነገር ግን እንደ ጠበቁት ሦስት ቀን የሞላው ጠረኑ የተቀየረ ሥጋ ሳይሆን ባዶ መቃብር ነበር ያገኙት፡፡ ማስተዋል አቅቷቸው እንጂ ጌታችን ከሞቱ አስቀድሞ “ይህንን ቤተ መቅደስ አፍርሱት በሦስተኛው ቀን አነሣዋለሁ” ብሎ በሥልጣኑ በሦስተኛው ቀን እንደሚነሣ ነግሯቸው ነበር፡፡ (ዮሐ.2፡18) በሌላም የወንጌል ክፍል “ያለ እኔ ፈቃድ ነፍሴን ከሥጋዬ የሚለያት የለም፤ እኔ ወድጄ እለያታለሁ እንጂ በመቃብር ላኖራት አዋሕጄም ላስነሣት ሥልጣን አለኝ፡፡” በማለት ስለሞቱና ስለ ትንሣኤው ተናግሮ ነበር፡፡ (ዮሐ.10፡18)

የጌታችን ሥጋ በመቃብር መፍረስ መበስበስን ሊያጠፋል ወደ መቃብር ወረደ እንጂ እስከ ክርስቶስ ድረስ በነበሩ ሙታን ሲሆን እንደነበረው መፍረስ መበስበስ ያለበት በሦስተኛውም ቀን ሽቱ መቀባት የሚያስፈልገው አይደለም፡፡ አይሁድ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ካንተ ምልክት ማየት እንሻለን ባሉት ጊዜ “አመጸኛና አመንዝራ ትውልድ ምልክትን ትሻለች ከነቢዩ ከዮናስ ምልክት በቀር ሌላ ምልክት አይሰጣትም፡፡ ዮናስ በአሳአንበሪ ሆድ ውስጥ ሦስት መዓልትና ሦስት ሌሊት እንደቆየ የሰው ልጅም በምድር ሆድ ውስጥ ሦስት መዓልትና ሦስት ሌሊት ይቆያል፡፡” በማለት መቃብር እንደማያስቀረው ሙስና መቃብርን አጥፍቶ በሦስተኛው ቀን እንደሚነሣ አስቀድሞ ተናግሮ ነበር፡፡ (ማቴ.12፡39)

ወደ መቃብሩ የሄዱ ሴቶች በተደጋጋሚ በሰሙት የአይሁድ የውሸት ወሬ ምክንያት አስቀድሞ የሰሙትን የጌታ የትንሣኤውን ነገር በሙሉ እምነት መቀበል አልቻሉም ነበርና ሽቱ ለመቀባት ሄዱ፡፡ በለሊት ከወንዶቹ ቀድመውና ጨክነው ወደ መቃብሩ የሄዱበት ጥንካሬ ግን የሚደንቅ ነው፡፡ ቀድመው በመሄዳቸው ቀድመው የትንሣኤውን ብስራት ሰሙ፤ በዓይናቸውም አይተው አረጋገጡ፡፡ ጌታችን ከሙታን መካከል እንደሌለ፣ መሞቱ ሞታችንን ሊያጠፋ፣ ወደ መቃብር መውረዱም በመቃብር ፈርሶ በስብሶ መቅረትን ሊያስወግድ እንደሆነ ተረዱ፡፡

የጌታችን የሞተው ሞታችንን ለመግደል የተነሣውም እኛን ለማሥነሳት ነውና የጌታችን ትንሣኤን ስናከብር የምናከብረው ትንሣኤያችንን እንደሆነ መረዳት ያስፈልጋል፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “ዘተሰቅለ በእንተ ኃጢአትነ ከመ ያጽድቀነ ወትንሥአ ከመ ያንሥአነ – ሊያጸድቀን ስለኃጢአታችን ተሰቀለ፤ ሊያነሣንም ተነሣ” ይላል፡፡ (ሮሜ.4፡25) ስለዚህ የትንሣኤን በዓል ስናከብር የተነሣንበት በዓል እያከበርን ነውና በዓሉ ሙት በሆነ ሕይወት እንዳናከብር በትንሣኤ ልቡና ተነሥተን ስለእኛ ሕይወት የተቆረሰውን የክርስቶስ ሥጋን በመብላት ደሙንም በመጠጣት ሊሆን ይገባል፡፡ በዓለ ትንሣኤ የመነሣት በዓል ነውና ለፍቅር ለአንድነት ለሰላም ከመነሣት ጋር በዓሉን ማክበር ይገባል፡፡

ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ “ወአድኃነነ በርደቱ እመስቀሉ ውስተ ሲኦል ወፈትሐ እለሀለዉ ሕየ ጻድቃነ ሙቁሐነ በኃጢአተ አዳም አቡሆሙ – ከመስቀሉ ወደ ሲኦል በመውረዱ አዳነን በዚያም በአባታቸው አዳም ኃጢአት ምክንያት የታሰሩ ጻድቃንን ፈታ፡፡ ብሎ እንዳስተማረ የምናከብረው በዓል የመፈታት በዓል ስለሆነ ከኃጢአት፣ ከክፋት ከዘረኝነትና መሰል እስራቶች ተፈትተን ልናከብረው ይገባል፡፡
በመጨረሻም በመላው ዓለም የምትገኙ ኦርቶዶክሳውያን፣ በሀገር ውስጥም ከሀገር ውጭም ያላችሁ በሰንበት ትምህርት ቤት የምታገለግሉ ወጣቶችና ሕጻናት በዓሉ ለንስኃ፣ ለአገልግሎትና ለመልካም ነገር የመነሣትና ከተለያዩ የዓለም እስራቶች የመፈታት በዓል እንዲሆንላችሁ እመኛለሁ፡፡

እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሳችሁ! መልካም የትንሣኤ በዓል ይሁንላችሁ!

መጋቤ ሐዲስ ጸጋ ወ/ትንሣኤ
በመ/ፓ/ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ሓላፊ

የሰ/ት/ቤቶች አንድነት የማኅበራዊ የትስስር ገጾችን ቤተሰብ ይሁኑ!

(የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት)

Youtube

https://www.youtube.com/@eotc-gssu

Facebook

https://www.facebook.com/gssu.eotc

Telegram

https://t.me/eotcgssu21

Tiktok

@eotc_gssu

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on LinkedIn
  • Share on Telegram
  • Share by Mail
https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/Tinsae.jpg 1280 886 Abenezer Mamushet https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/logo-2-1-300x74-1.png Abenezer Mamushet2025-04-20 20:53:152025-05-01 12:00:50“ኢሀሎ ዝየ ዳእሙ ተንሥአ በከመ ይቤ – ከዚህ የለም እንደ ተናገረው ተነሥቷል፡፡” ማቴ.28፡6
Search Search

Recent Posts

  • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ
  • ሦስተኛ ዙር የ፲፪ ክፍል ምርቃት መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት ተከናወነ።

Archives

  • April 2026
  • September 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • May 2025
  • April 2025
  • October 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • July 2022
  • June 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
© Ethiopian Orthodox Church Global Sunday School Union | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
  • Link to Youtube
  • Link to Telegram
  • Link to TikTok
Link to: ፵፫ኛው የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ተጀመረ Link to: ፵፫ኛው የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ተጀመረ ፵፫ኛው የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት... Link to: ወቅታዊ መልእክት Link to: ወቅታዊ መልእክት ወቅታዊ መልእክት
Scroll to top Scroll to top Scroll to top