የሰ/ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት በሁሉም አጥቢያዎች እንዲተገበር መመሪያ ተላለፈ

በዓለም አቀፍ ሰ/ት/ቤቶች አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ በተወሰነው ውሳኔ መሠረት ሁሉም አኅጉረ ስብከት ተዘጋጅቶ የቀረበውን የአንደኛ ክፍል መጻሕፍት ተግባራዊ እንዲያደርጉ ለሁሉም አኅጉረ ስብከቶች ከመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት ደብዳቤ ወጣ።

በዚህም መሠረት ሁሉም አኅጉረ ስብከት እስከ አጥቢያ በማሳወቅና ያልደረሳቸው እንዲደርሳቸው በማድረግ በትኩረት እንዲሠራ መመሪያ ተላልፏል፡፡

መጻሕፍቱን ለማግኘት ይህን ሊንክ ይጠቀሙ : ሥርዓተ ትምህርት

ስለ አተገባበር መልእክት ለመላክ የአንድነቱን የቴሌግራም ቻናል ይጠቀሙ