የአንደኛ ክፍል ፈተና ተሰጠ

በባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት የተሰጠው የአንደኛ ክፍል የአጋማሽ ዓመት ፈተና እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ በተሳካ ሁኔታ መጠናቀቁን የሀገረ ስብከቱ የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት አስታወቀ። ፈተናው እሑድ ፣ ታኅሣሥ 10 ቀን፣ 2014 ዓ/ም የተሰጠ ሲሆን፤ በሀገረ ስብከቱ በሚገኙ እና የአዲሱን ሥርዓተ ትምህርት ትግበራ ባስጀመሩ ሃያ ሰባት ሰንበት ት/ቤቶች የሚገኙ  አንድ ሺህ ሁለት መቶ አርባ ሰባት (1,247) ህጻናት ፈተናውን ወስደዋል።

ከነዚህም ሰንበት ት/ቤቶች መካከል ከፍተኛ ቁጥር ያለው ተማሪ በማስፈተን ቅድሚያውን የወሰዱ ሰንበት ት/ቤቶች የሚከተሉት ናቸው፦

  1. ምሥራቀ ፀሐይ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ሰ/ት/ቤት አንድ መቶ ሃያ አራት (124)  ህጻናት በማስፈተን፣
  2. መንበረ ስብሐት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ሰ/ት/ቤት አንድ መቶ አምስት (105) ህጻናት በማስፈተን፣
  3. የጽርሐ አርያም ደብረ ሲና በዓታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን ሰ/ት/ቤት ስድሳ ዘጠኝ (69) ህጻናትን በማስፈተን፣

ከዚሁ ጋር በማከልም በመጀመሪያው መንፈቀ ዓመት የትምህርት ክፍለ ጊዜ የሚሰጡት የትምህርት ዓይነቶች መሠረተ ሃይማኖት ፣ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናት እና የልሳነ ግእዝ  መሆናቸውን የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሰንበት ት/ቤቶች አንድነት አስታውቋል።