የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት - በኢ/ኦ/ተ/ቤ የመንበረ ፓትርያርክ ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ አንድነቱ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ተቋማዊ ራእይ፣ ተልእኮ
      • መዋቅራዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቋማዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማስፈጸሚያ
    • ስልታዊ እቅድ 2018 – 2021 ዓ/ም
  • ሥርዓተ ትምህርት
    • መሠረታዊ መረጃዎች
    • የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት አደረጃጀት መመሪያ
    • የሥርዓተ ትምህርቱ መመማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
    • የሥርዓተ ትምህርቱ ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ /ካሌንደር
    • የመምህራን ሥልጠና እና መልእክቶች
    • መጻሕፍቱን ለማግኘት እና ተጨማሪ መረጃ
    • ልዩ ልዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች
  • ፕሮጀክቶች
  • መዝሙረ ማኅሌት
    • የመስከረም ወር መዝሙሮች
      • የዮሐንስ መዝሙር
      • የመስቀል መዝሙሮች
      • የብዙኃን ማርያም መዝሙር (መስከረም ፳፩ )
      • የዘመነ ጽጌ መዝሙር
    • የጥቅምት ወር መዝሙሮች
      • የአብርሃ ወአጽብሐ መዝሙር (ጥቅምት 4 ቀን)
    • የኅዳር ወር መዝሙሮች
      • የቅዱስ ሚካኤል መዝሙር (ኅዳር 12 ቀን)
    • የጥር ወር መዝሙሮች
      • የዘመነ ጥምቀት መዝሙር
      • የቃና ዘገሊላ መዝሙር (ጥር 12 ቀን)
    • የመጋቢት ወር መዝሙሮች
      • የወርኃ ጾም መዝሙሮች
      • የሆሣዕና መዝሙራት
      • የሰሙነ ሕማማት መዝሙሮች
  • ዜና
    • አጫጭር ዜናዎች
    • ዝርዝር ዜናዎች
    • ወቅታዊ መረጃዎች
    • ማስታወቂያ
      • የሰንበት ትምህርት ቤቶች መጻሕፍት እንግሊዝኛ ትርጉም ሥራ ተሳትፎ ጥሪ
  • ያግኙን
  • ቋንቋ
    • ትግርኛ
    • Afaanoromo
  • Menu Menu

የቋሚ ኮሚቴዎች እና ንዑሳን ኮሚቴዎች የውስጥ አሠራር መመሪያዎች ትግበራ ሂደት ላይ ገለጻ ተሰጠ

በኢ/ኦ/ተ/ቤ መንበረ ፓትርያርክ የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት በመላው ዓለም ለሚገኙ ሰ/ት/ቤቶች የሚሰጠውን አገልግሎት ዘመኑን በዋጀ ተደራሽነት ወጥነት እና ዘላቂነት ባለው አሠራር ለመምራት እንዲያስችለው የሚያግዝ የቋሚ ኮሚቴዎች፣ የዋና ክፍሎች እና የንዑሳን ኮሚቴዎች የውስጥ አሰራር መመሪያ ረቂቅ ሰነድ መዘጋጀቱን ተከትሎ ትላንት እሁድ የሰነዶቹን የትግበራ ሂደት የሚዳስስ የግንዛቤ ማስጨበጫ ገለጻ ለሥራ አመራር አባላት መሰጠቱን የአንድነቱ ም/ሰብሳቢ ዲ/ን ስንታየሁ ምስጋናው ገለጹ።

አንድነቱ የመጀመሪያውን ዙር የመሪ ዕቅድ ትግበራ አጠናቆ በአሁኑ ወቅት በሁለተኛው ዙር የመሪ ዕቅድ ትግበራ ላይ እንደሚገኝ የገለጹት ም/ሰብሳቢው በዕቅድ ከተያዙት ተግባራት መካከል የሰ/ት/ቤ/ትን ተቋማዊ ጥንካሬ እና የአፈጻጸም ብቃት ያለንበት ነባራዊ ሁኔታ በሚጠይቀው ደረጃ ማሳደግ መሆኑን ጠቅሰዋል። እንደ ምክትል ሰብሳቢው ገለጻ የቋሚ ኮሚቴዎችን፣ የዋና ክፍሎችን እና የንዑሳን ኮሚቴዎችን የዕለት ተዕለት አፈጻጸም በወጥነት እና በዘላቂነት ለመምራት በጎ ፈቃደኛ ባለሙያዎችን በማሳተፍ የተዘጋጁት የውስጥ አሠራር መመሪያዎች የሙከራ ትግበራ ሂደት የሰ/ት/ቤት ተቋም ግንባታ ሂደት አካል ሲሆን ዝግጅቱ ሙሉ በሙሉ ተጠናቆ ትግበራ ሲጀመር አንድነቱ ለሰ/ት/ቤቶች ዘመኑን የዋጀ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችለውን ተቋማዊ ብቃት ለማጠናከር አንድ እርምጃ ወደፊት የሚያስኬደው መሆኑ ይታመናል። የተዘጋጁት መመሪያዎችም የሰ/ት/ቤቶች አንድነት ውስጣዊ አሠራር የተቋማዊ አሠራር መገለጫዎች የሆኑትን ወጥነትን፣ ዘላቂነትን እና የማያቋርጥ መሻሻልን ታሳቢ ያደረጉ እንደሆኑ እና በዓለም አቀፍ መልካም ተሞክሮዎች ላይ የተመሠረቱ ዘመናዊ የሥራ አመራር ጥበቦችን ያገናዘቡ እንደሆኑ ምክትል ሰብሳቢው ገልጸዋል።

የመመሪያዎቹ የትግበራ ሂደት የአንድነቱን የመዋቅር አካላት የዕለት ተዕለት እንቅስቃሴ ከግምት ውስጥ ያስገባ እና የተቀናጀ ትግበራ ስልት አሳላጭ መንገዶችን ያካተተ ሲሆን ይህንኑ ሂደት በዋናነት የሚመራ አጋዥ ኃይለ ግብር ግብረኀይል በማካተት በሙያው የካበተ ልምድ ባላቸው የሥራ አመራሩ አባላት እንዲመራ በቋሚ ኮሚቴ ደረጃ የተዋቀረ መሆኑን ለመረዳት ተችሏል። የቋሚ ኮሚቴው ኃላፊ እንደገለጹት ኮሚቴው የመጀመሪያውን የስድስት ወር መሰናዶ ዕቅድ በመንደፍ ሥራውን የጀመረ ሲሆን በቀጣይ ሂደቶችም ከመነሻ የትግበራ ሂደቱ የሚገኙትን ተሞክሮዎች መሠረት በማድረግ እና የአህጉረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት መዋቅር አካላትን በማሳተፍ በአህጉረ ስብከት ደረጃ ሥራ ላይ የሚውል ተመሳሳይ የውስጥ አሠራር መመሪያዎችን የማዘጋጀት እቅድ መኖሩ ገልጸዋል። የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አያይዘውም በመላው ዓለም የሚገኙ የአህጉረ ስብከት ሰ/ት/ቤቶች አንድነት መዋቅር አካላት ብሎም አጥቢያ ሰ/ት/ቤቶች በዚሁ ዙሪያ በመጪዎቹ ወራት በሚኖረው የትግበራ ሂደት እንዲሳተፉ እና የሚጠበቅባቸውን ግብዓት እንዲሰጡ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል።

በአንድነቱ የውስጥ አሠራር ማሻሻያዎች ዙሪያ ከተጠናቀቁት ተግባራት መካከል በያዝነው የትምህርት ዘመን መጀመሪያ የተለቀቀው የአንድነቱ ድረ ገጽ መሆኑን የገለጹት ምክትል ሰብሳቢው በቀጣይ ሂደቶችም በርካታ የተቋም ግንባታ ሥራዎች መታቀዳቸውን እና የሰ/ት/ቤቶች ተሳትፎ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ የሚበረታታ መሆኑን አስታውሰዋል።

በትግበራ ሂደቱ የግንዛቤ ማስጨበጫ ላይ ከተነሱት ነጥቦች መካከል ቤተ ክርስቲያናችን በአሁኑ ወቅት እያጋጠማት ያለውን ውጫዊ ፈተና ሰ/ት/ቤቶች በተሻለ ተቋማዊ አንድነት ላይ ቆመው ለመመከት የተቀናጀ፣ ዘላቂነት እና ወጥነት ያላቸው የውስጥ አሠራርን የሚያቀላጥፉ የተቋም ግንባታ መርሖዎችን መከተል እንደሚገባቸው ተገልጿል።

የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት መዋቅር ቤተ ክርስቲያን በሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መመሪያ በኩል የምትሠራውን ሥራ የበለጠ ዘመኑን በዋጀ መልኩ ተደራሽ ለማድረግ በጥቅምት ወር 2006 ዓ.ም በቅዱስ ሲኖዶስ ደረጃ መመሪያ ወጥቶለት ሥራ የገባ መዋቅር ነው፡፡ መዋቅሩም በዋናነት ሁሉም ሰንበት ት/ቤቶች ዘንድ ወጥ የሆነ የአገልግሎት ሥርዓት ከመዘርጋት በተጨማሪ ተተኪው ትውልድ ወጣቱ ከተናጠል አገልግሎት ተናባቢና ተልዕኮ መር አገልግሎት ውስጥ በሁሉም ዓለም ተደራሽ ለማድረግ ታሳቢ በማድረግ የተቋቋመ አደረጃጀት በመሆኑ ቅዱስ ሲኖዶስ በሰጠው ኃላፊነት መሠረት ይህ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚዘጋጀው የውስጥ መመሪያ፣ በአኅጉረ ስብከት፣ በወረዳ ቤተ ክህነትና በአጥቢያ ደረጃ በተመሳሳይ እየተዘጋጀ እንደሚወረድ ዕቅድ ተይዞ እየተሠራ መሆኑም ተገልጿል፡፡

ዘጋቢ፡  በግንኙነት ክፍል ቋሚ ኮሚቴ የውጭ ግንኙነት ዋና ክፍል የዜና እና ወቅታዊ መረጃዎች ዝግጅት ንዑስ ክፍል

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on LinkedIn
  • Share on Telegram
  • Share by Mail
https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/SSD-logo.jpg 640 640 gssu https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/logo-2-1-300x74-1.png gssu2022-02-09 00:02:482022-02-23 09:21:59የቋሚ ኮሚቴዎች እና ንዑሳን ኮሚቴዎች የውስጥ አሠራር መመሪያዎች ትግበራ ሂደት ላይ ገለጻ ተሰጠ
Search Search

Recent Posts

  • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ
  • ሦስተኛ ዙር የ፲፪ ክፍል ምርቃት መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት ተከናወነ።

Archives

  • April 2026
  • September 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • May 2025
  • April 2025
  • October 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • July 2022
  • June 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
© Ethiopian Orthodox Church Global Sunday School Union | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
  • Link to Youtube
  • Link to Telegram
  • Link to TikTok
Link to: መንፈሳዊ በዓል ለማክበር በወጡ ኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚደርስ ጥቃትን አጥብቀን እንቃወማለን Link to: መንፈሳዊ በዓል ለማክበር በወጡ ኦርቶዶክሳውያን ላይ የሚደርስ ጥቃትን አጥብቀን እንቃወማለን መንፈሳዊ በዓል ለማክበር በወጡ ኦርቶዶክሳውያን... Link to: እንኳን ለጾመ ነነዌ በሰላም አደረሳችሁ! Link to: እንኳን ለጾመ ነነዌ በሰላም አደረሳችሁ! እንኳን ለጾመ ነነዌ በሰላም አደረሳችሁ!
Scroll to top Scroll to top Scroll to top