የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት - በኢ/ኦ/ተ/ቤ የመንበረ ፓትርያርክ ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ አንድነቱ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ተቋማዊ ራእይ፣ ተልእኮ
      • መዋቅራዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቋማዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማስፈጸሚያ
    • ስልታዊ እቅድ 2018 – 2021 ዓ/ም
  • ሥርዓተ ትምህርት
    • መሠረታዊ መረጃዎች
    • የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት አደረጃጀት መመሪያ
    • የሥርዓተ ትምህርቱ መመማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
    • የሥርዓተ ትምህርቱ ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ /ካሌንደር
    • የመምህራን ሥልጠና እና መልእክቶች
    • መጻሕፍቱን ለማግኘት እና ተጨማሪ መረጃ
    • ልዩ ልዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች
  • ፕሮጀክቶች
  • መዝሙረ ማኅሌት
    • የመስከረም ወር መዝሙሮች
      • የዮሐንስ መዝሙር
      • የመስቀል መዝሙሮች
      • የብዙኃን ማርያም መዝሙር (መስከረም ፳፩ )
      • የዘመነ ጽጌ መዝሙር
    • የጥቅምት ወር መዝሙሮች
      • የአብርሃ ወአጽብሐ መዝሙር (ጥቅምት 4 ቀን)
    • የኅዳር ወር መዝሙሮች
      • የቅዱስ ሚካኤል መዝሙር (ኅዳር 12 ቀን)
    • የጥር ወር መዝሙሮች
      • የዘመነ ጥምቀት መዝሙር
      • የቃና ዘገሊላ መዝሙር (ጥር 12 ቀን)
    • የመጋቢት ወር መዝሙሮች
      • የወርኃ ጾም መዝሙሮች
      • የሆሣዕና መዝሙራት
      • የሰሙነ ሕማማት መዝሙሮች
  • ዜና
    • አጫጭር ዜናዎች
    • ዝርዝር ዜናዎች
    • ወቅታዊ መረጃዎች
    • ማስታወቂያ
      • የሰንበት ትምህርት ቤቶች መጻሕፍት እንግሊዝኛ ትርጉም ሥራ ተሳትፎ ጥሪ
  • ያግኙን
  • ቋንቋ
    • ትግርኛ
    • Afaanoromo
  • Menu Menu

እርሱን የምሾመው ለመንበሩ ክብር እንዲሰጠው ነው

እርሱን የምሾመው ለመንበሩ ክብር እንዲሰጠው ነው

እርሱን የምሾመው ለመንበሩ ክብር እንዲሰጠው ነው

ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ “አሁንም በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁ ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። ከእኔ በኋላ ለመንጋዪቱ የማይራሩ ነጣቂዎች ተኵላዎች እንደሚመጡ እኔ አውቃለሁ። ደቀ መዛሙርትንም ወደ እነርሱ ይመልሱ ዘንድ ጠማማ ትምህርትን የሚያስተምሩ ሰዎች ከእናንተ መካከል ይነሣሉ። ስለዚህም ትጉ፤ እኔ ሁላችሁንም ሳስተምር ሦስት ዓመት ሙሉ ሌትም፣ ቀንም እንባዬ እንዳልተገታ አስቡ። አሁንም ለእግዚአብሔርና ሊያነጻችሁ በቅዱሳንም ሁሉ መካከል ርስትን ሊሰጣችሁ ለሚችለው ለጸጋው ቃል አደራ ሰጥቻችኋለሁ” (ሐዋ. ፳÷ ፳፰-፴፪)¹ በማለት ያስተማረው ትምህርት ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ኤጲስ ቆጶሳትን ስትመርጥ በጣም እንድትጠነቀቅ የሚያሳስብ ቃል ነው።

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ለጳጳሳት ምርጫ የምትጨነቀውም ለመንጋው የማይራሩ ክፉዎች ተሾመው ምእመናንን ከእግዚአብሔር እንዳያራርቋቸው ነው። ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን የጳጳሳት ምርጫ የሚያሳስባት ዓላማው ሰማያዊ፣ ተልእኮው ሰውን ለመንግሥተ ሰማያት ማብቃት በመሆኑ ነው። ጳጳሳት ኖላዊ መሆናቸውን የተረዱ አባቶችም መንበራቸው ክፍት በሆኑ አህጉረ ስብከት ላይ የሚመድቧቸው አባቶች ማንነት ያሳስባቸዋል። ጉዳዩ አሳሳቢ የሚሆንበት የመጀመሪያው ምክንያት ለጵጵስና የሚመረጡ አባቶች ምግባረ ብልሹ ከሆኑ ሰዎችን ለድኅነት ማብቃት ሲገባቸው ከድኅነት ስለሚያርቋቸው ነው። ሁለተኛው ምክንያት ደግሞ በእነርሱ ምግባረ ብልሹነት ቤተ ክርስቲያን  እንዳትተች ነው። እንዲህ ያሉ አባቶች ቢመረጡ ክርስቲያኖችን የሚፈልጓቸው ለጊዜያዊ ነገር መጠቀሚያነት ብቻ ይሆናል ።

የክህነትን ተግባር በሚገባ የተረዳው ታላቁ አባት ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ ቀጰዶቅያንና አካባቢውን ግኖስቲኮችና አርዮሳውያን ተቈጣጥረውት በነበረበት ዘመን የሁለቱንም ወገኖች ኑፋቄ ከሥሩ ነቅሎ ለመጣል በመንፈሳዊ ሕይወታቸውም፣ በዕውቀታቸውም የተመሰከረላቸውን አባቶች እየመረጠ በተጓደሉ መናብርት ላይ ሲያስቀምጥ ወንድሙን ቅዱስ ጎርጎርዮስን ዐሥራ ሦስት ክርስቲያን ቤተ ሰቦች ብቻ ይገኙባት በነበረችው ኑሲስ በምትባለው ሀገረ ስብከት ሊሾመው መሆኑን የተረዱ ሰዎች ወደ ቅዱስ ባስልዮስ ቀርበው “ቅዱስ ጎርጎርዮስን ያህል ታላቅ አባት እዚህ ግባ በማትባል ከተማ እንዴት ትሾመዋለህ? በሚል ላቀረቡለት ጥያቄ ቅዱስ ባስልዮስ ሲመልስ ወንድሜን በኑሲስ የሾምኩት ከመንበሩ መዓርግና ክብር እንዲያገኝ ሳይሆን ለመንበሩ መዓርግና ክብር እንዲያመጣለት ነው ” በማለት መልስ ሰጥቷል።²

ቅዱስ ባስልዮስ የኦርቶዶክስ ሃይማኖትን ሊያቀኑ፣ ከአርዮሳውያንም ሊጠብቁ የሚችሉ ሊቃውንትን እንዲፈልግ ያስገደደው በኑፋቄ በመታወራቸው ምክንያት ለመንጋው የማይራሩ ሰዎች መንበሩ ላይ ተቀምጠው ክርስቲኖችን እንዳያሳስቱ ነው። ዘመኑም እንደ ወርቅ የጠሩ ኦርቶዶክሳውያን በመብራት ተፈልገው የሚገኙበት የመከራ ዘመን ነበር። ሰዎች በብዙ ድካም ታላቅ ባደረጉት ሀገረ ስብከት ላይ ተሾሞ መቀመጥ የሚያሳየው የተተኪውን ታላቅነት ሳይሆን ሰዎች በደከሙበት መግባቱን ነው። “ነቢያት በገረገሩት ሐዋርያት ማገሩት” የሚባለውም አንዱ በደከመበት ሌላው ሲገባ ነው። ቅዱስ ባስልዮስ የመረጠው ግን ወንድሙ ደክሞ መንበሩን ታላቅ እንዲያደርገው ስለነበር ትንቢቱ ተፈጽሟል፤ አሳቡም ተሳክቷል።

ቅዱስ ባስልዮስ ስለ ቅዱስ ጎርጎርዮስ የተናገረው በተግባር መፈጸሙን ግብፃዊው ቄስ ያዕቆብ ማላቲ “ስብከት ድኅረ ዘመነ ሐዋርያት” በተሰኘ መጣጥፋቸው “Itissaid thatwhenSt. GregoryofNyssawasordainedas abishoptherewereonly13familiesinhisdiocese,and onhis departure fromthis world there wereonly 13 pagan families፡- ቅዱስ ጎርጎርዮስ ጵጵስና ተሹሞ ወደ ኑሲስ በሄደ ጊዜ በሀገረ ስብከቱ የነበሩ ዐሥራ ሦስት ክርስቲያን ቤተሰቦች ሲሆኑ ሌሎቹ ኢአማንያን ነበሩ። ቅዱሱ አባት ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፎ ወደ አምላኩ ሲጠራ በሀገረ ስብከቱ ክርስትናን ያልተቀበሉት ዐሥራ ሦስት ቤተሰቦች ብቻ ነበሩ”³ ብለዋል።

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አባቶችን ለኤጲስ ቆጶስነት ስትመርጥ መመሪያዋ ለመንበሩ ክብር የሚሰጡትን በመፈለግ እንጂ ምድራዊ ሀብት በተትረፈረፈባቸው አህጉረ ስብከት በመሾማቸው ክብር ለማግኘት የሚደክሙትን ለመመደብ መሆን የለበትም የሚባለውም ለዚህ ነው። የአባትነት ስሙን ብቻ ይዘው በግብሩ የማይገኙትን፣ የባለሥልጣናትን መዓድ ለመባረክ አገረ ስብከታቸውን ትተው በመዞር ቤተ ክርስቲያን እንድትተች ምክንያት የሚሆኑትን መመደብ ክርስቲያኖች ወደ መንግሥተ ሰማያት እንዳይገቡ በሩን እንደ መዝጋት ይቈጠራል።

መማለጃ በመስጠት ወይም ኤጲስ ቆጶስ ከመሆን የሚገባቸውን አባቶች ፈልገው እንዲያቀርቡ ቅዱስ ሲኖዶስ ኃላፊነት የተሰጣቸውን አባቶች ደጅ በመጥናት ካላሾማችሁኝ የሚሉትንና ታላቁ ቅዱስ ጳውሊ እንደ ቁራ ጠቁረው ባያቸው ጊዜ ያለቀሰላቸውን አይነት ሰዎች መምረጥ አይገባም። እንዲህ ያሉት በስም እንጂ በግብር አባት መባል አይገባቸውምና። እንዲህ ያሉ ሰዎች ቢሾሙም የቤተ ክርስቲያንን ቍጥርንም፣ የክርስቲያኖችን ምግባርንም ስለማያሻሽሉ የሚሾሙት አባቶች ለመንበሩ ክብር የሚሰጡት፣ ክርስቲያኖችን ለምግባርና ትሩፋት እንዲነሣሡ ምክንያት የሚሆኑት ብቻ መሆን ይገባቸዋል።

 

ማጣቀሻ መጻሕፍት

  1. የኢትዮጵያ መጽሐፍ ቅዱስ ማኅበር፣ መጽሐፍ ቅዱስ፤ ብሉያትና ሐዲስ ኪዳን መጻሕፍት፣ (፳፻ ዓ.ም.)
  2. ዳንኤል ክብረት፣ መንፈሳዊ ሕይወት ምንድን ነው?ሕይወቱ ለሙሴ፣ ( ፲፱፻፺፱ ዓ.ም.)
  3. FR.Tadros Y, Malaty, Preaching in the post Apostolic Era. (2002)
Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on LinkedIn
  • Share on Telegram
  • Share by Mail
https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/lemenberu-kbr.jpg 1080 1920 Abenezer Mamushet https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/logo-2-1-300x74-1.png Abenezer Mamushet2023-06-27 21:08:212023-06-28 12:50:28እርሱን የምሾመው ለመንበሩ ክብር እንዲሰጠው ነው
Search Search

Recent Posts

  • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ
  • ሦስተኛ ዙር የ፲፪ ክፍል ምርቃት መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት ተከናወነ።

Archives

  • April 2026
  • September 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • May 2025
  • April 2025
  • October 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • July 2022
  • June 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
© Ethiopian Orthodox Church Global Sunday School Union | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
  • Link to Youtube
  • Link to Telegram
  • Link to TikTok
Link to: ኤጲስ ቆጶስ ለመሾም የሚያገለግለው መስፈርት Link to: ኤጲስ ቆጶስ ለመሾም የሚያገለግለው መስፈርት ኤጲስ ቆጶስ ለመሾም የሚያገለግለው መስፈርት Link to: የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ሂደት ላይ ያለውን ጥያቄ በደብዳቤ አሳወቀ Link to: የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በኤጲስ ቆጶሳት ምርጫ ሂደት ላይ ያለውን ጥያቄ በደብዳቤ አሳወቀ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በኤጲስ ቆጶሳት...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top