የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት - በኢ/ኦ/ተ/ቤ የመንበረ ፓትርያርክ ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ አንድነቱ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ተቋማዊ ራእይ፣ ተልእኮ
      • መዋቅራዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቋማዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማስፈጸሚያ
    • ስልታዊ እቅድ 2018 – 2021 ዓ/ም
  • ሥርዓተ ትምህርት
    • መሠረታዊ መረጃዎች
    • የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት አደረጃጀት መመሪያ
    • የሥርዓተ ትምህርቱ መመማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
    • የሥርዓተ ትምህርቱ ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ /ካሌንደር
    • የመምህራን ሥልጠና እና መልእክቶች
    • መጻሕፍቱን ለማግኘት እና ተጨማሪ መረጃ
    • ልዩ ልዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች
  • ፕሮጀክቶች
  • መዝሙረ ማኅሌት
    • የመስከረም ወር መዝሙሮች
      • የዮሐንስ መዝሙር
      • የመስቀል መዝሙሮች
      • የብዙኃን ማርያም መዝሙር (መስከረም ፳፩ )
      • የዘመነ ጽጌ መዝሙር
    • የጥቅምት ወር መዝሙሮች
      • የአብርሃ ወአጽብሐ መዝሙር (ጥቅምት 4 ቀን)
    • የኅዳር ወር መዝሙሮች
      • የቅዱስ ሚካኤል መዝሙር (ኅዳር 12 ቀን)
    • የጥር ወር መዝሙሮች
      • የዘመነ ጥምቀት መዝሙር
      • የቃና ዘገሊላ መዝሙር (ጥር 12 ቀን)
    • የመጋቢት ወር መዝሙሮች
      • የወርኃ ጾም መዝሙሮች
      • የሆሣዕና መዝሙራት
      • የሰሙነ ሕማማት መዝሙሮች
  • ዜና
    • አጫጭር ዜናዎች
    • ዝርዝር ዜናዎች
    • ወቅታዊ መረጃዎች
    • ማስታወቂያ
      • የሰንበት ትምህርት ቤቶች መጻሕፍት እንግሊዝኛ ትርጉም ሥራ ተሳትፎ ጥሪ
  • ያግኙን
  • ቋንቋ
    • ትግርኛ
    • Afaanoromo
  • Menu Menu

ክርስትና ከዘውግ ባሻገር የሆነ ማንነት

ክርስትና ከዘውግ ባሻገር የሆነ ማንነት

ክርስትና ከዘውግ ባሻገር የሆነ ማንነት

የሰው ልጅ ሁሉ ከአዳም የተገኘ የእግዚአብሔር አምላክ የእጅ ሥራ ነውና ከላይ በቀለም በቅርፅ ወዘተ ልዩነት ቢኖረው እንኳ የሚመሳሰልበት ከውስጥ የሆነ ሥነ-ሕይወታዊ አንድነት አለው፡፡ ይህም ተመሳሳይ ተፈጥሮአዊ እና ሥነ ልቡናዊ (Bio-Psychic Union) ውቁር እንዲኖረው አድርጓል፡፡ በማኅበራዊ ፍጡርነቱ በፈጠረው በማኅበራዊ መስተጋብሩ ምክንያት ደግሞ በሒደት ራሱን ካንድ የባህል መሠረት ካለው ማንነት ጋር ያዛምዳል፡፡ ይህ ልዩነት ደግሞ የተለያየ አስተሳሰብ/ እና የአረዳድ አድማስ እንዲኖረው ያደርገዋል፡፡ ክርስትና ለነፍሳችን መድኅን የሆነው የእውነትና የሕይወት መንገድ ጌታችን መድኃኒታችን ክርስቶስ ኢየሱስ ብቻ መሆኑን ያስተምራል፡፡ ክርስቲያንም ይህን እውነት ብቻ ይከተላል፡፡ ከአምልኮ መልስ ባለው ማኅበራዊ መስተጋብር ግን ብዝኃነትን ያከብራል፡፡
ክርስትና የባህል ማንነትን ሳይጨፈልቅና ባህል የፈጠረውን የቋንቋ እና የአኗኗር ዘይቤ ህላዌነት ካላጠፋሁ ሳይል ህያዊት ለሆነች የሰው ልጆች ነፍስ ዘላለማዊ ዕረፍት ለመስጠት ከእውነተኛው አምላክ በእግዚአብሔር የተበረከተ መለኮታዊ መገለጥ ነው፡፡ የሰው ልጆች ሁሉ የመጡበት የተለያየ ማኅበራዊ ዳራ ዓለምን ለማዳን ከድንግል ማርያም ሰው በሆነው በእግዚአብሔር ልጅ ከማመን እስካልከለከላቸው ድረስ ሰማያዊ ዜግነት ከሚያስገኘው ክርስትና የሚለያቸው አንዳች ነገር አይኖርም፡፡ ክርስቲያን ሆነው ከምእመናን ኅብረት ለመደመር የፈጠራቸውን ኋላም ሰው ሆኖ በደሙ ያዳናቸውን አምላክ ማመንና ለእርሱ መስከር እንጂ የባህል ማንነታቸውን መወርወር አያስፈልጋቸውም፡፡
በ፶፩ ዓ.ም. በቅዱስ ያዕቆብ ሊቀ መንበርነት በኢየሩሳሌም የጉባኤዎች ሁሉ መሠረት ተደርጎ በሚቆጠረው የመጀመሪያው የሐዋርያት ጉባኤ የተወሰነውም ይኸው እውነት ነው፡፡ ክርስትና አንዱ ብቻውን በባለቤትነት ሊይዘው የማይችል፣ የዘርና የባህል ማንነትን የተሻገረ፣ ሁሉም የእኔ የሚለው፣ ለሁሉም ሕይወትን የሚሰጥ መንገድ መሆኑን የተረጋገጠበት ታላቅ ጉባኤ ነበር፡፡ በኢየሩሳሌም ሳሉ ክርስትናን መርጠው አይሁድነትን ተሰናብተው የመጡት እና አሕዛብነት ንቀው ወደ ዕረፍት ውኃ የገቡት የትመጣቸው ወይም የኖሩበት የባህል ዳራ ወደ ፉክክርና ንትርክ ገፍቷቸው ነበር፡፡ ሕዝብን ከአሕዛብ አንድ ባረገው ጌታ እያመኑ የቀደመ ልዩነታቸውን ተከትለው ድንበር ሊያሠምሩ ፈለጉ፡፡ ጉባኤተኞቹ ግን የሰውን ሳይሆን የእግዚአብሔር ወልድን አሰረ ፍኖት የተከተሉት፣ ጌታ ነፍስን ከሥጋ፣ ሕዝብን ከአሕዛብ፣ ሰማይን ከምድር እንዳስታረቀ ምስክር የሆኑት ሐዋርያት ነበሩ፡፡ እናም አይሁዳዊውን እሳቤ ገሥጸው አሕዛባዊውን ልማድ ከርክመው ለቅዱሳን አንድ ጊዜ በተሰጠች በአንዲት ሃይማኖት ጥላ ሥር ተሰባስበው የሚኖሩበትን ሥርዓት ሠሩላቸው፡፡ ይህም በክርስትና ልጅና ባርያ እንደሌለ ሁሉም እኩል በልጅነት ጸጋ እንደከበረ እንዲታወቅና ነገድ ተኮር ዘውገኝነት እና ስብከት በክርስትና ቦታ እንዳይኖረው አድርጓል፡፡
ለሰማያዊ ዜግነት የሚሮጥ መንፈሳዊ ሯጭ ደመናን የማይሻገረው ምድራዊ ማንነት አይበልጥበትም፡፡ ቀራኒዮ ላይ የተከፈለው ዋጋ አይሁድ ከግሪክ ሳይለይ፣ ያለ አድልኦ ለሕዝብና ለአሕዛብ የተከፈለ
ከጉባኤው በኋላም ከአይሁድነት አዳኙን መሲሕ ወደ ማመን የመጡት ወገኖች አይሁዳዊነታቸው ሙሉ ለሙሉ ተገፍፎ አልወደቀም፡፡ ለግዝረትና ለሌሎች የኦሪት ሕጎች ያላቸው መቆርቆር በተወሰነ መጠን አብሯቸው ነበረ፡፡ ነገር ግን ለክርስትና ያላቸው ከፍተኛ ቀናዒነት ለምሥራቃዊዋ ኮከብ አንጾኪያ ነዋሪዎች ጎልቶ የታየ እውነት ነበረ፡፡ የመጀመሪያውን የሲኖዶስ ጉባኤ ውሳኔ ለመተግባር ያሳዩት መትጋት ከኦሪት ይልቅ ለሐዲስ ኪዳን ያላቸውን መንበርከክ ያመላክታል፡፡ ከአሕዛብ ወገን ወደ ክርስትና የገቡትንም ኅሩያን መሆናቸው፣ የመንገዱ ተከታይነታቸው ሕይወታቸውን በበጎ ለውጦታል፡፡
በኢየሩሳሌም አይሁድ በክርስቲያኖች ላይ በክፉ ተነሡባቸው፡፡ ክፋታቸው ከብዶ ከሰባቱ ዲያቆናት አንዱ የነበረውን ትጉሑን አገልጋይ እስጢፋኖስን በድንጋይ ወግረው ገደሉ፡፡ በምድር በክርስትና ሰማዕታት ታሪክ ቀዳሚ ገጽ ላይ (ገጽ አንድ ላይ) የቀዳሚው ሰማዕተ ጽድቅ ታሪክ ተከተበ፡፡ በአርያም በሰማያዊ መዝገብ ላይ ስሙ በማይጠፋ ቀለም ተጻፈ፡፡ የአይሁድ ጭከና ክርስቲያኖችን አስደንግጦ የመጀመሪያውን ስደት ወለደ፡፡ ወደ አንጾኪያ ተሰደዱ፡፡ ሲሰደዱ ሐዋርያት በጉባኤው የሠሩላቸውን ሥርዐት ይዘው ነው የተሰደዱት፡፡
በአይሁድ አኗኗር ውስጥ ጎልቶ ይታይ የነበረው የአሕዛብን ልምድ የመጸየፍ ትምክህት ሰው ሁሉ በአርአያ ሥላሴ የተፈጠረ ነው በሚለው ክርስቲያናዊ የሥነ ሰብ አስተምህሮ ረግቧል፡፡ የሰውን ልጅ ሁሉ በእኩል ዐይን ልጄ ወዳጄ በሚለው በክርስቶስ ፍቅር ተሸንፏል፡፡ በአሕዛብ ዘንድ የነበረው አይሁድን የመናቅና የመጠራጠር አባዜም እርስ በእርሳችሁ ተዋደዱ በሚለው ክርስቶሳዊ ትምህርት ተገርቷል፡፡ ይህን ያስተዋሉ አንጾኪያውያን ደቀ መዛሙርቱን አይሁድና ግሪካዊ ማለት ትተው የክርስቶስ ወገን ናቸው ሲሉ ክርስቲያኖች በማለት ሰየሟቸው፡፡ ተግባራቸው ወገናቸውን ተናገረ፡፡ አዲሱ ዘውግ ያመነ የተጠመቀን ሁሉ የሚቀበል የቋንቋና ባህል፣ የድንበርና ዘር አጥር ያልከለለው የቀራንዮን ማኅተም የያዘ ሁሉ ውግንና የሚያገኝበት ኅብረት ነው፡፡ የክርስቶስ በሆነው መጠራት ታላቅ ጌጥ እንደ ሆነ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ተናግሯል፡፡
የጌታ ደቀ መዛሙርት ክርስቶሳዊነታቸውን ብርቱ በሆነ ልሳን ዘወትር የሚመሰክረውን ክርስቲያን የተሰኘውን የወል ስያሜ መጀመሪያ ያገኙት የመጡበትን ማኅበረሰባዊ ማንነት አሽቀንጥሮ መጣል ሳያስፈልጋቸው ነገር ግን በጋራ ወይም የሁሉ ከሆነው ሕዝብን ከአሕዛብ፣ አይሁዳዊውን ከግሪካዊው ካስተሣሠረው ክርስቲያናዊ ማንነት በታች ማድረጋቸው ከተረጋገጠ በኋላ ነው፡፡ ደቀ መዛሙርት መጀመሪያ ክርስቲያኖች (የክርስቶስ ወገን) የተባሉት በአንጾኪያ ነው ብለናል፡፡ በኖሩበት፣ ከጌታ አንደበት በተማሩበት በኢየሩሳሌም ሳይሆን የተማሩትን በተግባር በኖሩበት አንጾኪያ ክርስቲያን ተባሉ፡፡ ይህ ልብ ላለው ኦርቶዶክሳዊ ሁሉ ክርስቲያን ተብሎ የክርስቶስ በሆነው ለመጠራት ክርስትናውን ዋነኛ መገለጫው አድርጎ መቀበል እና በዚያ መኖር እንዳለበት ይገነዘባል፡፡

እነኛ የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች አሕዛብን ወደ ክርስትና የሳቡት በቃልና በሕይወት በማስተማር ነው፡፡ ስለ ፍቅር ይናገራሉ ሰውን ሁሉ ያለ ልዩነት የወደደውን አምላክ አርአያ ተከትለው ፍቅራቸውን ለሁሉ ይገልጻሉ፡፡ ከዝሙት፣ ከአምላኮ ጣዖት፣ የሰውን ክብር ከሚያዋርዱ ተግባራት፣ በዘመኑ በሮማ ግዛት ገንኖ ከነበረውና ክቡሩን ሰው በኮሎዚየም አደባባይ ውስጥ ከሚያጨፋጭፈው እንስሳዊ ተግባር ሁሉ እጅግ የሚገርም ተዐቅቦ ነበራቸው፡፡ ይህ አኗኗራቸው ደመ ነፍሳዊነት በተንሰራፋበት አሕዛባዊው የማኅበረሰብ መስተጋብር ውስጥ እንደ ዕንቁ ተለይተው እንዲያበሩ አድርጓቸዋል፡፡ እንስሳዊነት የተጣባው ትርጉም የለሽ አኗኗር የሰለቻቸውና እንደ ሰው የክብር ሕይወት ኖረው መሞት የሚፈልጉ አሕዛብ ሁሉ ነገረ-ክርስትናን እና የክርስቲያኖችን አኗኗር በቅርብ መከታተል ቀጠሉ፡፡ ክርስትና ሰዎች ትርጉም ላለው እና ከፍ ላለ ግብ ሰብአዊነትን ተላብሰው፣ ትርጉም ያለው አኗኗር የሚኖሩበት ሕይወት መሆኑን ከቃላቸውና ከተግባራቸው ሲረዱ ወደ ክርስትና በብዛት መግባት ጀመሩ፡፡ ለመጀመሪያ ጊዜ ብዙ አሕዛብ ስመ ውልድና ያገኙትም በአንጾኪያ ነበር፡፡
በአንጾኪያ ያሉ አሕዛብ የጌታን ተከታዮችን ውሎ አዳር ዐዩ፤ በእርስ በእርስ መስተጋብራቸው ያለውን መዋደድ አስተዋሉ፡፡ በመካከላቸው ያለው ባህላዊ ልዩነት ሳያግዳቸው እንደ ወንድምና እኅት ሲተሳሰቡ ተመለከቱ፡፡ እናም ከነባር ነገዳዊ ማንነታቸው በላይ አዲስ ፍጥረት ላደረጋቸው ክርስትና የነበራቸው ልባዊ አቀባበል ክርስቲያን አስባላቸው፡፡ ለዚህ ነው ዘውግ ተኮር ሃይማኖታዊ ስብከት ፈጽሞ ክርስቲያናዊ መሆን የማይችለው፡፡ አንድ ክርስቲያን በክርስትናው ያገኘው መንፈሳዊ ኅብረት ሰው ሠራሽ ከሆነው ባህልና ቋንቋ ያገኘው ማንነት ከበለጠበት ከክርስትና ጎዳና ውጭ ሆኗል፡፡ በክርስትና ጀልባ ተሳፍረን የተሻገረርነውን ንዑስ ማንነታችንን ከፍ ያለ ጸጋ ከሚያሰጠው ክርስቲያናዊ ማንነታች ካስበለጥነው ክርስትናችን ከወዴት አለ?
ክርስቲያን የሚለው ስም ከአንድ የባህል ማንነት ለተቀዳ ወገን ብቻ የተሰጠ መጠሪያ አይደለም፤ ሆኖም ዐያውቅም፡፡ በክርስቶስ ኢየሱስ ለአመኑ፣ በስመ ሥላሴ ተጠምቀው አዲሱን ተፈጥሮ ገንዘብ ያደረጉ የሰው ልጆች ሁሉ የተጎናጸፉት ሰማያዊ እና ዘላለማዊ ጸጋ ነው፡፡ ይህ ከውኃና ከመንፈስ ዳግም በመወለድ የተገኘ ማንነት ሰዎች ቀድሞ ከነበራቸው ከየትኛውም ሰዋዊ ማንነት በላይ የከበረና ከሰማይ በታች የማይቀር ስምና ማንነት ነው፡፡
ከድሮም የጌታችን የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ደቀ መዛሙርት ክርስቲያን የሚለውን መጠሪያ ያገኙት ተናጠላዊው የባህል ወይም የነገድ ማንነታቸው የጋራ ለሆነው ክርስቲያናዊ ማንነታቸው ተሸንፎ እጅ ከሰጠ በኋላ ነው፡፡ ይህ ግሩም የሆነ በስሙ የመጠራት ጸጋ ዓለምን ሁሉ ያለ አድልኦ እንዲሁ በመውደድና ለሰው ዘር ሁሉ ሕይወቱን በመስጠት የተቤዠን ጌታ በተጓዘበት ፍኖት በመጓዝ የተገኘ ጸጋ ነው፡፡ ይህ ከነገድ ሳይሆን የነገድ ፈጣሪውን ሰውን በፈጠረ አምላክ ስም የመጠራት ክብር የጌታን መርሕ ለተከተሉ ደቀ መዛሙርት በአንጾኪያ ተሰጠ፡፡ እኛም በዚሁ በክርስቶስ ሥጋ እና ደም ያገኘነው ፍጹም አንድነት ከጎሳም ሆነ ከባህል ማንነታችን በላይ አድርገን አክብረን እንይዘው ዘንድ ክርስቲያኖች ተብለን በስሙ ተጠራን፡፡
ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ክርስቲያንነት የማንነቶቻችን ሁሉ አክሊል መሆኑን ሲገልጽ እንዲህ ይላል፤ ‹‹ሰው ማንነቱን ሲጠይቁት ‹እኔ ክርስቲያን ነኝ!› ብሎ ከመለሰ ሁሉን በአንድ ላይ ዐውጇል፡፡ ሀገሩን፣ ሙያውን፣ ቤተሰቡን፡፡…››

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on LinkedIn
  • Share on Telegram
  • Share by Mail
https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/ክርስትና.jpg 1080 1920 Abenezer Mamushet https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/logo-2-1-300x74-1.png Abenezer Mamushet2023-11-07 21:43:112023-11-07 21:43:11ክርስትና ከዘውግ ባሻገር የሆነ ማንነት
Search Search

Recent Posts

  • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ
  • ሦስተኛ ዙር የ፲፪ ክፍል ምርቃት መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት ተከናወነ።

Archives

  • April 2026
  • September 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • May 2025
  • April 2025
  • October 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • July 2022
  • June 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
© Ethiopian Orthodox Church Global Sunday School Union | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
  • Link to Youtube
  • Link to Telegram
  • Link to TikTok
Link to: ነፋስን ዘርተዋል፤ ዐውሎ ነፋስንም ያጭዳሉ (ሆሴ. ፰፡፯) Link to: ነፋስን ዘርተዋል፤ ዐውሎ ነፋስንም ያጭዳሉ (ሆሴ. ፰፡፯) ነፋስን ዘርተዋል፤ ዐውሎ ነፋስንም ያጭዳሉ (ሆሴ.... Link to: ባይተዋርነት እስከ መቼ? Link to: ባይተዋርነት እስከ መቼ? ባይተዋርነት እስከ መቼ?
Scroll to top Scroll to top Scroll to top