የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና የሞዴልና ማጠቃለያ ፈተና ለመፈተን ዝግጅቱን ማጠናቀቁን የሀገር አቀፍ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት አሳወቀ።

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሰንበት ትምህርት ቤቶች አንድነት በትግበራ ላይ በሚገኘው ሥርዓተ ትምህርት መሠረት ተምረው ለምዘናው የተዘጋጁ ሰንበት ተማሪዎችን የመመዘኛ ፈተና ለመስጠት መዘጋጀቱን አስታወቀ።

ለምዘናው የሚቀርቡ አጥቢያ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በ2015ዓ.ም በሀገረ ስብከት ደረጃ የተዘጋጀውን የ10ኛ ክፍል መመዘኛ ፈተና ወስደው 12ኛ ክፍል የደረሱ ሰንበት ተማሪዎችን ሲሆን ለዚህም አስፈላጊውን መረጃ የመሰብሰብ አጥቢያዎችን የመለየት ሥራ መሥራቱን አንድነቱ አስታውቋል።

አንድነቱ በዘገባው የሞዴል ፈተናው የፊታችን ሰኔ 22 ቀን 2017 ዓ.ም የሚሰጥ ሲሆን ዋናውና ማጠቃለያ ፈተናው ደግሞ በአምስት የፈተና ማዕከላት ሐምሌ 27 የሚሰጥ መሆኑን ተናግሯል።