ከየሀገረ ስብከቱ ለተውጣጡ የሰንበት ትምህርት ቤት መምህራን የክረምት የአሠልጣኞች ሥልጠና ለመስጠት ዝግጅቱን ማጠናቀቁን የሰ/ት/ቤቶች አንድነት አስታወቀ።
የሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምርያ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት በዓመቱ መጨረሻ ከየሀገረ ስብከቱ ለተውጣጡ መምህራን የአሠልጣኞች ሥልጠና በማዘጋጀት አሠልጥኖ ወደየ ሀገረ ስብከታቸው ለአገልግሎት የማሰማራት ሥራ በየዓመቱ ሲያከናውን ቆይቷል። በዘንድሮም ዓመት ከ23 ሀገረ ስብከት በላይ ለተውጣጡና መመዘኛውን ለሚያሟሉ ከ200 በላይ ሠልጣኞች ሥልጠና ለመስጠት ቅድመ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አንድነቱ አስታውቋል።
ሥልጠናው የሚሰጠው በቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ዩንቨርስቲ ሲሆን ሠልጣኞች በቆይታቸው በተመረጡ ርዕሰ ጉዳዮች ዕውቀትን የሚያጎለብቱ፣ የግንዛቤ ለውጥ የሚያመጡ፣ ክህሎታቸውንም የሚያዳብሩ ሥልጠናዎች እንደሚሰጣቸውና ወደ ሀገረ ስብከታቸው ሲመለሱ በሥርዓተ ትምህርት ትግበራው ሰፊ ሥራ እንደሚሠሩ የሰ/ት/ቤቶች አንድነት አስታውቋል።