የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት - በኢ/ኦ/ተ/ቤ የመንበረ ፓትርያርክ ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ አንድነቱ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ተቋማዊ ራእይ፣ ተልእኮ
      • መዋቅራዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቋማዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማስፈጸሚያ
    • ስልታዊ እቅድ 2018 – 2021 ዓ/ም
  • ሥርዓተ ትምህርት
    • መሠረታዊ መረጃዎች
    • የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት አደረጃጀት መመሪያ
    • የሥርዓተ ትምህርቱ መመማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
    • የሥርዓተ ትምህርቱ ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ /ካሌንደር
    • የመምህራን ሥልጠና እና መልእክቶች
    • መጻሕፍቱን ለማግኘት እና ተጨማሪ መረጃ
    • ልዩ ልዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች
  • ፕሮጀክቶች
  • መዝሙረ ማኅሌት
    • የመስከረም ወር መዝሙሮች
      • የዮሐንስ መዝሙር
      • የመስቀል መዝሙሮች
      • የብዙኃን ማርያም መዝሙር (መስከረም ፳፩ )
      • የዘመነ ጽጌ መዝሙር
    • የጥቅምት ወር መዝሙሮች
      • የአብርሃ ወአጽብሐ መዝሙር (ጥቅምት 4 ቀን)
    • የኅዳር ወር መዝሙሮች
      • የቅዱስ ሚካኤል መዝሙር (ኅዳር 12 ቀን)
    • የጥር ወር መዝሙሮች
      • የዘመነ ጥምቀት መዝሙር
      • የቃና ዘገሊላ መዝሙር (ጥር 12 ቀን)
    • የመጋቢት ወር መዝሙሮች
      • የወርኃ ጾም መዝሙሮች
      • የሆሣዕና መዝሙራት
      • የሰሙነ ሕማማት መዝሙሮች
  • ዜና
    • አጫጭር ዜናዎች
    • ዝርዝር ዜናዎች
    • ወቅታዊ መረጃዎች
    • ማስታወቂያ
      • የሰንበት ትምህርት ቤቶች መጻሕፍት እንግሊዝኛ ትርጉም ሥራ ተሳትፎ ጥሪ
  • ያግኙን
  • ቋንቋ
    • ትግርኛ
    • Afaanoromo
  • Menu Menu

፵፫ኛው የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ተጀመረ

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን በየዓመቱ የሚደረገው የመንበረ ፖትርያርክ የጠቅላይ ቤተክህነት ፵፫ኛው የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤበዛሬው ዕለት ተጀመረ። በመክፈቻው ጉባኤ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያት ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት “እንደ ዐስራ ኹለቱ ሐዋርያት መንጋውን ትጠብቁት ዘንድ መንገዱን አሳምሩ” በሚለው በቅዱስ ያሬድ ቃል ተነስተው በሁለት ጉዳዮች ላይ ያተኮረ መልዕክትን አስተላልፈዋል።

የመጀመርያው መልዕክታቸው አስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ ሲሆን “በዚህ ዘመን በሐዋርያት መንበር ላይ ለመንጋውና ለመንግሥተ እግዚአብሔር የተሾምን እንደመሆናችን በመልካም አስተዳደርና በቀና እምነት ልናስተዳድር ይገባል። በአሁን ሰዓት የቤተክርስቲያን አስተዳደር ችግር በብዛት የሚስተዋልበት እንደመሆኑ ይህን ችግር ለመቅረፍ በጥናት ላይ በመመስረት በፍጥነት መስራት ይጠበቅብናል” ብለዋል።

ኹለተኛው መልዕክታቸውም የምዕመናንና የአገልጋዮች ሰቆቃና ሞት ላይ ያተኮረ ነው። በምዕመናንና በአገልጋዮች ላይ እስከ አሁኗ ሰዓት እያጋጠመ ያለውና ያልተቋረጠው እንግልትና ሞት እንደ ምሳሌ በምስራቅ ሸዋ ከነቤተሰቦቻቸው የተገደሉትን አባት በማንሳት እንዲህ አይነቱ ተግባር ሊቆም እንዲገባ መልዕክትን በማስተላለፍ ስብሰባው በይፋ መጀመሩን አብስረዋል።

በመቀጠል ብፁዕ አቡነ አብርሃም የጠቅላይ ቤተክህነት ዋና ሥራ አስኪያጅ፣ የባሕርዳርና ምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የሰበካ ጉባኤን ጅማሮና አሁን እስካለበት ድረስ ያለውን ታሪክ በማንሳት ይህን ሥርዓት ላበጁ አባቶች ክብርና ለዚህ ያደረሰንን አምላክ ልናመሰግን ይገባል ብለዋል። በመቀጠልም የመንበረ ፖትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የተከናወኑ ዋና ዋና ሥራዎችን ሪፖርት አቅርበዋል።

ጉባኤውም እስከ ጥቅምት 10 የሚቀጥል ሲሆን የየሀገረ ስብከቶችን የሥራ ሪፖርትና በተለያዩ ጉዳዮች ውሳኔ ይተላለፍበታል ተብሎ ይጠበቃል።

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on LinkedIn
  • Share on Telegram
  • Share by Mail
https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/logo-2-1-300x74-1.png 0 0 Abenezer Mamushet https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/logo-2-1-300x74-1.png Abenezer Mamushet2024-10-14 12:26:012024-11-21 19:43:00፵፫ኛው የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተክህነት የሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ተጀመረ
Search Search

Recent Posts

  • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ
  • ሦስተኛ ዙር የ፲፪ ክፍል ምርቃት መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት ተከናወነ።

Archives

  • April 2026
  • September 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • May 2025
  • April 2025
  • October 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • July 2022
  • June 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
© Ethiopian Orthodox Church Global Sunday School Union | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
  • Link to Youtube
  • Link to Telegram
  • Link to TikTok
Link to: እንደሚታረዱ በጎች ሆንን! Link to: እንደሚታረዱ በጎች ሆንን! እንደሚታረዱ በጎች ሆንን! Link to: “ኢሀሎ ዝየ ዳእሙ ተንሥአ በከመ ይቤ – ከዚህ የለም እንደ ተናገረው ተነሥቷል፡፡” ማቴ.28፡6 Link to: “ኢሀሎ ዝየ ዳእሙ ተንሥአ በከመ ይቤ – ከዚህ የለም እንደ ተናገረው ተነሥቷል፡፡” ማቴ.28፡6 “ኢሀሎ ዝየ ዳእሙ ተንሥአ በከመ ይቤ – ከዚህ...
Scroll to top Scroll to top Scroll to top