የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት - በኢ/ኦ/ተ/ቤ የመንበረ ፓትርያርክ ሰ/ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ
  • ቀዳሚ ገጽ
  • ስለ አንድነቱ
    • መሠረታዊ መረጃዎች
      • ተቋማዊ ራእይ፣ ተልእኮ
      • መዋቅራዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ተቋማዊ አደረጃጀት
      • የሰንበት ት/ቤቶች የሥራ አመራር ምርጫ ማስፈጸሚያ
    • ስልታዊ እቅድ 2018 – 2021 ዓ/ም
  • ሥርዓተ ትምህርት
    • መሠረታዊ መረጃዎች
    • የሰንበት ት/ቤቶች ሥርዓተ ትምህርት አደረጃጀት መመሪያ
    • የሥርዓተ ትምህርቱ መመማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
      • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
    • የሥርዓተ ትምህርቱ ዓመታዊ የጊዜ ሰሌዳ /ካሌንደር
    • የመምህራን ሥልጠና እና መልእክቶች
    • መጻሕፍቱን ለማግኘት እና ተጨማሪ መረጃ
    • ልዩ ልዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች
  • ፕሮጀክቶች
  • መዝሙረ ማኅሌት
    • የመስከረም ወር መዝሙሮች
      • የዮሐንስ መዝሙር
      • የመስቀል መዝሙሮች
      • የብዙኃን ማርያም መዝሙር (መስከረም ፳፩ )
      • የዘመነ ጽጌ መዝሙር
    • የጥቅምት ወር መዝሙሮች
      • የአብርሃ ወአጽብሐ መዝሙር (ጥቅምት 4 ቀን)
    • የኅዳር ወር መዝሙሮች
      • የቅዱስ ሚካኤል መዝሙር (ኅዳር 12 ቀን)
    • የጥር ወር መዝሙሮች
      • የዘመነ ጥምቀት መዝሙር
      • የቃና ዘገሊላ መዝሙር (ጥር 12 ቀን)
    • የመጋቢት ወር መዝሙሮች
      • የወርኃ ጾም መዝሙሮች
      • የሆሣዕና መዝሙራት
      • የሰሙነ ሕማማት መዝሙሮች
  • ዜና
    • አጫጭር ዜናዎች
    • ዝርዝር ዜናዎች
    • ወቅታዊ መረጃዎች
    • ማስታወቂያ
      • የሰንበት ትምህርት ቤቶች መጻሕፍት እንግሊዝኛ ትርጉም ሥራ ተሳትፎ ጥሪ
  • ያግኙን
  • ቋንቋ
    • ትግርኛ
    • Afaanoromo
  • Menu Menu

ባይተዋርነት እስከ መቼ? ክፍል ሁለት

ባይተዋርነት እስከ መቼ? ክፍል ሁለት

ባይተዋርነት እስከ መቼ? ክፍል ሁለት

በክፍል አንድ ጽሑፋችን ኦርቶዶክሳውያን በሀገራችን ባይተዋር ያደረጉንን ጥቂት ምክንያቶች ለማየት ሞክረናል፡፡ በዛሬው ጽሑፋችን ደግሞ ከዚህ ባይተዋርነት የመውጫ መንገዶችን ለመጠቆም እንሞክራን፡፡
1. ለሰማያዊ ክብር፣ ለዘላለማዊ ሕይወት የሚያበቃ መንፈሳዊ ዝግጅት ይኑረን፡- እንደ ቃሉ የምንኖር እምነተ ብርቱዎች እና ከምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን በአግባቡ የምንካፈል መሆን አለብን፡፡ ይህ መንፈሳዊ ዝግጅት እንደ ጥንቶቹ ጽኑ ክርስቲያኖች በአሕዛብ ፊት ያለ ፍርሃት “እኛ የተሰቀለውን ክርስቶስን እንሰብካለን” የምንል የዐደባባይ ምስክሮቹ እንድንሆን ያበረታናል፡፡ “ልንሔድ ከክርስቶስ ጋር ልንኖር እንናፍቃለን” ለማለት ያበቃናል፡፡ በቤተ ክርስቲያን ላይ የሚፈጸመውን በደል ለመቃወም እና ፍትሕ ርትዕ ለመጠየቅ ብሎም ለማስፈን እንድንችል፣ የፍርሃትን መንፈስ ገድለን የኃይልና የሥልጣንን መንፈስ እንድንለብስ ያደርገናል፡፡
2. መከራን በአኮቴት እንቀበለው እንጂ አንልመደው፤
እንደ አንድ ክርስቲያን እንዴት ባለ አኗኗር እንኖር ዘንድ እንዲገባን መመሪያችን ቅዱስ መጽሐፍ ነው፡፡ ቅዱሱን መጽሐፍ በሕይወታቸው የኖሩትን ቅዱሳን ሕይወት ደግሞ እንደ ወደብ ማኅቶት ከሩቅ እየተመለከትነው ወደ እዚያ እንቀዝፋለን፡፡ ይህን በራስ ፍላጎት ክብርን ፍለጋ ራስን ዝቅ በማድረግ ትሕትና እና ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም የመኖርን ጥበብ በረከት እያገኘንበት ልንቀጥል የምንችለው ግን የእውነት መንገድ በስፍራው እስካለ ድረስ ነው፡፡ ስለዚህ የተወረወረብንን ጦር፣ የተወነጨፈብንን ቀስት አድራሻ መለየት ግድ ይለናል፡፡ “የግል ሕይወቴን ሊፈታተን የመጣ መከራ ነው ወይስ የማምነውን እምነት ዝክረ ስም ለማጥፋት የተነቀነቀ ጦር?” ብለን መጠየቅ ይኖርብናል፡፡ “የሚምዘገዘገው ጦር ዒላማ የሆንኩት እኔ እንደ አንድ ክርስቲያን በእምነቴ እየተፈተንኩበት ነው ወይስ መጭው ትውልድ እንደ ክርስቲያን እንዳይኖር የክርስትናን ዘር ለማጥፋት የታለመ ነው?” የሚለውን መመለስ ይገባናል።
ከላይ ላነሣነው ጥያቄ የምንሰጠው መልስ መከራው በአኮቴት የሚቀበሉት ነው ወይስ ጋሻ አንሥተው ሊመክቱት የሚገባ ነው የሚለውን ውሳኔ ለመስጠት ይረዳናል፡፡ ለክብር በአኮቴት የምንቀበለው መከራ ህልውናን ለሚፈታተን የበለጠ አሣር አሳልፎ እንዳይሰጠን ማስተዋል የተገባ ነው፡፡ እንደ ቀላል በሆደ ሰፊነት የምናልፋቸው ጥቃቶች ሌላ ጥቃት እየወለዱ ሰፊ መቃብር ውስጥ እየከተቱን እንደሆነ የሚታይ ነገር ነው፡፡
አንዱን ፍርሃት እና ታካችነት ተደራርበው የሰፈሩበት ሰው የከጓደኛው ጋር በተኛበት ሌሊት ጅብ ይመጣና እግሩን መብላት ይጀምራል፡፡ ጓደኛው ‹‹አረ ምንድን ነው የመጣብን?›› ብሎ እንዲነቃ ሲቀሰቅሰው፡፡ “ዝም በል ጅብ የእኔን እግር እየበላ ነው፤” ብሎ እየመጣ ያለውን መከራ ረስቶ እንዲያንቀላፋ መከረው፡፡ እንዲህ ዓይነቱ ምክር ራስን የማዳኛውን ጊዜ ቆርጥሞ የሚበላ ከፍርሃት እና የአጥቂህን አልጠግብ ባይነት ካለማወቅ የሚወለድ ከንቱ ምክር ነው፡፡
ኦርቶዶክሳውያን እየሆነብን ያለውን መከራ ለምደነዋል፤ ወይም በኦርቶዶክሳውያን ሕይወት ላይ የተቃጣው ዱላ ዳር ሀገር ባሉት ወገኖቻችን ትከሻ ላይ ብቻ የሚበርድ መስሎናልና በምን ግዴ ቸል ብለነዋል፡፡ ክርስቲያናዊ ወንድማማችነት ተዘንግቶ፣ አንዱ በእምነት ለሚመስለው ወንድሙ መቆምን ትቶ ነገዳዊ ውግንናን መሰባሰቢያ ማንነታችን አድርገነዋል፡፡ ሰዎኛው የዘውግ ፖለቲካ ከአጽራረ ቤተ ክርስቲያን ሴራ ጋር ተጋምዷል፡፡ ለዘመናት የተሠራንበት የክርስትና ሥሪት ነገዳዊ ዘውገኝነትን መቋቋም አቅቶት ወደ ፍርስራሽነት ከተቀየረ አዲሱ ትውልድ በክርስትና መርሕ እና እሴቶች ታንፆ የማደግ ዕድሉም አብሮ ይፈራርሳል፡፡ ይህም የኢትዮጵያችን እስትንፋስ ሆኖ የኖረውን የክርስትና ሐረግ የሚበጠስ ነው፡፡
3. የኦርቶዶክሳዊነት ጋሻ ለመሆን ዝግጁ የሆነ ሥነ ልቡና ያስፈልጋል፡፡ በሕገ ልቡና፣ በሕገ ኦሪትና በሕገ ወንጌል እግዚአብሔርን በማምለክ የኖሩ አበው እና እማት ልጆች ነን፡፡ ገና በክርስትና የጧት ዘመናት ከሕገ ኦሪት በጃንደረባው ቅዱስ ባኮስ በኩል ‹‹የሚመራኝ ሳይኖር ይህ እንዴት ይቻለኛል?›› በማለት የመንፈስ ቅዱስን ምሪት ጠይቃ፣ ኢየሱስ ክርስቶስ የእግዚአብሔር ልጅ እንደ ሆነ አምናለሁ በማለት ጥምቀትን የተቀበለች ሀገር ዜጎች ነን፡፡ ክርስትናን በመቀበል እና ብሔራዊ ሃይማኖት አድርገን በማወጅ ከቀዳሚዎቹ ተርታ ነን፡፡ ዛሬ ይህ ሁሉ በኢትዮጵያ ምድር እንኳን በእውን ሲተገበር በታሪክ ዓምድ ላይ ተጽፎ እንዲቀመጥ የተፈለገ አይመስልም፡፡ ይህን የጠላት ሐሳብ ለመዋጋት የተዘጋጀ ኦርቶዶክሳዊ መሆን ይጠበቅብናል፡፡
4. ዓለምን በንቃት መከታተል፤ የመልክዐ ምድራዊ ፖለቲካ እና ማኅበረ ኢኮኖሚያዊ ለውጦች በሕዝበ ክርስቲያኑ ላይ የሚያሳድሩትን አሉታዊም ሆነ አዎንታዊ ተጽእኖ የሚገመግም የሁነት ትንተና የሚሠራ ክፍል (ዲፓርትመንት) እንዲኖር ማድረግ ለነገ የማይባል ተግባር ነው፡፡ ይህ ክፍል ሁሉን አቀፍ ዓቅምና ቁርጠኝነቱ ያላቸው የቤተ ክርስቲያኗ ልጆች የሚሳተፉበት፣ አስፈላጊው የሰው ኃይልና ሀብት የተሟላለት ሊሆን ይገባል፡፡ በአዎንታዊ ዕድሎች ለቤተ ክርስቲያን ሐዋርያዊ ትልእኮ ስኬት መጠቀም የሚቻልበትን፣ አሉታዊ ለውጦችን የተጽእኖ አድማስ ማዳከም የሚቻልበትን ምክረ ሐሳቦች በጥናት ተመሥርቶ ያቀርባል፡፡
5. ዓለም አቀፍ ትኩረት ለማግኘት መሥራት፡- ኦርቶዶክሳውያንን ዒላማ ያደረገ እና የተራዘመ ጥቃት መኖሩን ማሳወቅ፤ በክርስትናችን ምክንያት ለጥቃት መጋለጣችንን በኦርቶዶክሰዊያን ላይ እየደረሰ ያለውን የሰብአዊ መብት ጥሰት ይመለከተዋል ለሚባል ተቋም በማማረጃ አስደግፎ ማሳየት ተገቢ ነው፡፡

Share this entry
  • Share on Facebook
  • Share on X
  • Share on WhatsApp
  • Share on LinkedIn
  • Share on Telegram
  • Share by Mail
https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/baytewar-2.jpg 1080 1920 Abenezer Mamushet https://eotc-gssu.org/a/wp-content/uploads/logo-2-1-300x74-1.png Abenezer Mamushet2023-12-06 21:07:502023-12-06 21:07:50ባይተዋርነት እስከ መቼ? ክፍል ሁለት
Search Search

Recent Posts

  • የሦስተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የኹለተኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የአንደኛ ክፍል መማሪያ መጻሕፍት ይዘት
  • የመስቀል ደመራ በዓል በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ
  • ሦስተኛ ዙር የ፲፪ ክፍል ምርቃት መርሐ ግብር ብፁዕ አቡነ ዮሐንስ በተገኙበት ተከናወነ።

Archives

  • April 2026
  • September 2025
  • August 2025
  • July 2025
  • June 2025
  • May 2025
  • April 2025
  • October 2024
  • December 2023
  • November 2023
  • October 2023
  • September 2023
  • August 2023
  • July 2023
  • June 2023
  • May 2023
  • February 2023
  • January 2023
  • December 2022
  • November 2022
  • October 2022
  • September 2022
  • July 2022
  • June 2022
  • April 2022
  • February 2022
  • January 2022
  • October 2021
  • September 2021
© Ethiopian Orthodox Church Global Sunday School Union | Website by atbiya.com
  • Link to Facebook
  • Link to Youtube
  • Link to Telegram
  • Link to TikTok
Link to: በረሃብ ከመሞት በጦርነት መሞት ይሻላል Link to: በረሃብ ከመሞት በጦርነት መሞት ይሻላል በረሃብ ከመሞት በጦርነት መሞት ይሻላል Link to: እንደሚታረዱ በጎች ሆንን! Link to: እንደሚታረዱ በጎች ሆንን! እንደሚታረዱ በጎች ሆንን!
Scroll to top Scroll to top Scroll to top